ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ)

(if you can't read our Amharic pages, please download the font here: Visual Geez Unicode)

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል የሲታዊ መንፈሳዊነትን መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

 
ራድዮ ቫቲካን- ክርስትና የሚያበስረው ደኅንነት የምንወደውን ዘለዓለማዊ ሕይወት እንጂ የማይጨበጥ ደኅንነት ኣይደለም
ቅዱስ ኣባታችን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትናንትና ረፋድ ላይ ለዕረፍት ከሚገኙበት ካስተል ጋንደልፎ ሓዋርያዊ አዳራሽ የመልኣከ እግዚአብሔር ጸሎት ከማሳረጋቸው በፊት ‘እመቤታችን ድንግል ማርያም እንደ ክርስቶስ ልጇ ሞትን አሸንፋ በነፍስዋና በሥጋዋ በሁለመናው ሰማያዊ ክብር እንደተጐናጸፈች እናምናለን’ ሲሉ በላቲኑ ሥርዓተ ኣምልኮ ከ5 ቀናት በፊት የተዘከረውን የፍልሠታ በዓል የተመለከተ ትምህርት ሰጥተዋል።
የፍልሠታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የሚከተለዉን ስብከት ሰብከዋል።

Last Updated (Friday, 20 August 2010 12:26)

 

ራድዮ ቫቲካን - እሑድ እኩለ ቀን ላይ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎትን ሲያሳርጉ ባሰሙት ስብከት፣ የእንተ ላእለ ኵሉ (ካቶሊካዊት) ቤተ ክርስያን ካህናት በሰው ልጅ ታሪክ ለመንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኅዳሴ መረጋገጥ የደረሷቸው መጻሕፍት፣ የሰጡት አብነት እና አስተዋጽኦ የማይካድ ብቻ ሳይሆን የሚደነቅ መሆኑን   አመልክተዋል።

በመቀጠልም ለአንድ ዓመት በኵላዊት ቤተ ክርስትያን የተከበረውንና ባለፈው ሳምንት የተጠናቀቀውን የክህነት ዓመት መዝጊያ ምክንያት በማድረግ ከመላ ዓለም የተወጣጡ ከ15 ሺሕ በላይ የሚገመቱ ካህናት የተሳተፉበት በሮማ የተካሄደው ዓቢይ በዓል ፈጽሞ የማይረሳ የዘወትር ትውስታ እንደሚሆን ገልጠው፣ በዚህ የክህነት ዓመት ምክንያት እግዚአብሔር ለኵላዊት ቤተ ክርስትያን ለሰጠው ጸጋዎች ምስጋናን በማቅረብ፣ የታደሉት ጸጋዎች ማንም ሊለካው የማይቻል ቢሆንም ፍሬው በግልጽ የታየና ገና ተትረፍርፎ የሚታይ ነው ብለዋል።

ካህን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልብ ለቤተ ክርስትያን እና ለዓለም የሰጠው እና የሚሰጠው ጸጋ መሆኑም አስረድተው፣ ካህናትን የፍቅር ሥልጣኔ የመጀመሪያ አገልጋዮች በማለትም ገልጠዋቸዋል። ቅዱስ ዮሓንስ ማሪያ ቪያነይ እና ባለፈው ሳምንት ቅድስት ቤተ ክርስትያን በቫርሳቪያ ብፅእና ያወጀችለት የደም ሰማዕት የፖላንድ ተወላጅ ካህን ኣባ ጀርዝይ ፖፒየሉስዝኮን በመጥቀስ ለክህነት ሕይወት አብነት ናቸው ካሉ በኋላ፣ ቅዱስ አባታችን መላው ውሉደ ክህነትን ለቅድስት ድንግል ማርያም ጥበቃ በማማጸን፣ ባለፉት ጥቂት ቀናት ቅድስት ቤተ ክርስትያን ብፅእና ያወጀችላቸውን በማሰብ፣ በተለይም ደግሞ ዓለማዊ ምእመን ጋዜጠኛ ማኑኤል ሎዛኖ ጋሪዶ፣ ሕመም እና ስቃይ ሳይበግረው፣ ሥራውን እና ክርስትያናዊ ኃላፊነቱን በመወጣት የመሰከረው እምነት በቅድሱ ቁርባን ላይ የነበረው ፍቅር የሕይወቱ ማእከል በማድረግ የኖረው ለሁሉም ጋዜጠኞች አብነት ነው ብለው፣ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰው በብዙ ሺሕ ለሚገመተው ምእመን ቡራኬ በመስጠት መልካም እሁድን ተመኝተው የዕለቱን አስተምህሮ አጠቃለዋል።

Last Updated (Tuesday, 15 June 2010 13:06)

 
የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 8:
Netherlands flag 23%Netherlands (3)
United Kingdom flag 23%United Kingdom (3)
Ethiopia flag 15%Ethiopia (2)
Latvia flag 8%Latvia (1)
Moldova, Republic of flag 8%Moldova, Republic of (1)
Sweden flag 8%Sweden (1)
United States flag 8%United States (1)
Unknown flag 8%Unknown (1)
13 visits from 8 countries