Tuesday 09 Feb 2010
  • Narrow screen resolution
  • Wide screen resolution
  • Wide screen resolution
  • Increase font size
  • Default font size
  • Decrease font size
እኛ ማነን...

(if you can't read our Amharic pages, please download the font here: Visual Geez Unicode)

Jesus-Nicodemus

"ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤ እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።" (ዮሐ.3:20-21) - ዘወረደ


በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል የሲታዊ መንፈሳዊነትን መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን። 1ጴጥ.4:11

 
ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ላይ የግድያ ሙከራ ያደረገው ቱርካዊ ከማረምያ ቤት ወጣ PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Wednesday, 20 January 2010 19:24

alg_pope_agcaIndependent Catholic News - Tuesday, January 19, 2010 - በ1973 ዓ.ም. በር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ላይ የግድያ ሙከራ ያደረገው ቱርካዊ ከእስር ተለቀቀ። ግለሰቡ ከዚህ በኋላ የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ግዳጁን እንደሚፈጽምም የቱርክ መገናኛ ብዙኀን ዘግቧል።

በአሁኑ ሰዓት 52 ዓመት ዕድሜ ያለው መህሜት አሊ አጅካ በር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ላይ ባደረገው የግድያ ሙከራ በጣልያን 19 ዓመታትን በእስር ያሳለፈ ሲሆን፤ በመቀጠል ደግሞ ከዚያ በፊት የአንድ ጋዜጣ አርታዒን በመግደሉ ሌላ 10 ዓመታትን በመታሰሩ በድምሩ 30 ዓመታት በእስር ቤት ማሳለፉ ታውቋል።

ምንም እንኳ በወቅቱ በቁጥጥር ሥር ሲውል ከማንም ጋር ትብብር የሌለው ግላዊ ድርጊት መሆኑን ቢገልጽም፤ ር.ሊ.ጳጳሳትን ለመግደል ለአጅካ ምክንያት የሆነው ነገር እስካሁን ምስጢር እንደሆነ ቀርቷል። በአንድ ወቅት የቱርክ አንድ አገራዊ ቡድን አባል የነበረ ሲሆን፤  በሌላ አጋጣሚም በቡልጋርያ የደኅንነት አገልግሎት እንደሚመራ ገልጾ የነበረ ቢሆንም እንኳ በ1970ዎቹ በጣልያን 22 ወራትን የፈጀው ምርመራ መረጃ ሳያገኝለት ቀርቷል።

በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የግድያ ሙከራ የተደረገባቸው ር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ በ1975 ዓ.ም. ከአጅካ ጋር ከተገናኙ በኋላ ይቅር ማለታቸው ይታወቃል።

በተደጋጋሚ የሚታዩት ኃይለኛ ቁጡነቱና "አዲስ መሲሕ ነኝ" የሚሉት ንግግሮቹ ስለአጅካ የአእምሮ ጤነኝነት ጉዳይ ቀጣይ የሆነ ጥያቄ አስነሥተዋል። ትላንትና ከእስር ሲለቀቅ ባደረገውም ንግግር "የዓለምን ፍጻሜ አውጄያለሁ፤ በያዝነው ክፍለ ዘመን መላው ዓለም ይወድማል፤ ሁሉም ሰውም ይሞታል። እኔ ዘላለማዊው ክርስቶስ ነኝ" ሲል ተደምጧል።

Last Updated on Wednesday, 20 January 2010 21:19
 
የልደተ ክርስቶስ ድባብ በቫቲካን መንበረ ጴጥሮስ PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Saturday, 09 January 2010 07:12

የልደተ ክርስቶስ ድባብ በቫቲካን መንበረ ጴጥሮስ አደባባይና ቤተ ክርስቲያን...(ፎቶዎች)

በቫቲካን ከተማ የሚገኘው የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ደብር - መንበረ ቅዱስ ጴጥሮስ - በዓለማችን ካሉ ተጎብኚ ቦታዎች የብዙዎችን ቀልብ በመሳብ ቀዳሚው መሆኑ ይታወቃል። ከአደባባዩ ጀምሮ እስከ ደብሩ ሥነ ሕንፃው ቅርጽና ውበት፣ እንዲሁም በውስጡ ያሉ  ዓለማችን ያፈራቻቸው ታላላቅ ሥነ ጥበብት የሳሏቸውና የቀራረጿቸው የጥበብ ሥራዎች፣ የተለያዩ ታሪካዊ ሰነዶችና ንዋየ ቅዱሳት...ወዘተ በተለያየ መልኩ ብዙ ሰዎች በቦታው ሲገኙ ከጊዜና ቦታ ውጭ የሆነ ወደሚመስል ስሜት ፈጥነው እንዲሻገሩ ያደርጋቸዋል።

ከነዚህ ተያዥና ተጨባጭ ነገሮች ባሻገር ለመላው ክርስቲያኖች በተለይም ደግሞ ለካቶሊካውያን ክርስቶስ ቅዱስ ጴጥሮስን እኔም እንዲህ እልሃለሁ፦ ጴጥሮስ አንተ ዓለት ነህ፤ በዚህችም የመሠረት ድንጋይ ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፤ ይህችንም ቤተ ክርስቲያን የሞትኃይል እንኳ አያሸንፋትም። እነሆ ለአንተ የመንግሥተ ሰማይን መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር ያሰርከው በሰማይ የታሰረ ይሆናል፤ በምድር የፈታኸው በሰማይ የተፈታ ይሆናል ማቴ.16:17-19 በማለት ሰማይና ምድር ቢያልፉ እንኳ በማያልፍ ቃሉ የሰጠውን ተስፋ ተቀብሎ እስከ ሰማዕታዊ ሞቱ ድረስ ለክርስቶስ የኖረው ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ የተቀበረበትና ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ ይህን የርሱን ኃላፊነት ያለማቋረጥ በመቀባበል በመተግበር ላይ ያሉ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሚቀመጡበት ስፍራ ስለሆነ የእግዚአብሔር ጸጋ ልዩ ሞገስን ያላበሰው ደብር መሆኑን አብዛኛው ሰው የሚመሰክረው እውነታ ነው።

ከዚህ በታች የሚመለከቷቸው ፎቶዎች ከላይ የገለጽነውን እውነታ ለማስተላለፍ አቅም ባይኖራቸውም፤ የዘንድሮውን የክርስቶስን ልደት በዓል -ገና- ምክንያት በማድረግ በቫቲካን ቅዱስ ጴጥሮስ ደብርና አደባባይ የተዘጋጀውን ጌታ ሲወለድ የነበረውን ድባብ የሚያሳይ ዝግጅት ለማሳየት እንሞክራለን። ወንጌሉ እንደሚለው በከብቶች መመገቢያ ግርግም ውስጥ በመላእክት፣ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና በቅዱስ ዮሴፍ መታጀቡን፤ በእረኞችና በነገሥታት መጎብኘቱን...ያሳያሉ። መልካም ቆይታ።

ክፍል 1 - የቅዱስ ጴጥሮስን ቤተ ክርስቲያን ከውስጥ በኩል በመጠኑ የሚያሳዩ ፎቶዎች (ይጫኑት)

ክፍል 2 - የቅዱስ ጴጥሮስን ቤተ ክርስቲያን ከውጭ በኩል የሚያሳዩ ፎቶዎች (ይጫኑት)

Last Updated on Monday, 18 January 2010 22:09
 
ተስፋችን እግዚአብሔር ነው PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Tuesday, 05 January 2010 07:27
ቫቲካን ሬድዮ - (03-01-2010) - ቅ.ኣ.ር.ሊ.ጳ ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትናንትና በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡት ምእመናንና ነጋድያን የዕለቱን ቃለ ወንጌል በመጥቀስ “የሰው ልጅ ታሪክ በእግዚአብሔር መለኮታዊ ጥበብ ስለሚመራ ትርጉም አለው” በማለት ታሪካችን አቅጣጫና ዓላማ ያለው እንጂ በዘፈቀደ የሚሄድና በጥንቈላዊና በምጣኔ ሃብታዊ ትንቢቶች የሚወሰን አለመሆኑን አብራርተው የመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎትን አሳረገዋል።

ትምህርታቸውም እንደሚከተለው ነው፣ ውድ ወንድሞቼና እኅቶቼ፦...

 
ማንም ሰው ብቻውን እንዳይሆን፤ ማንም ሰው እንዳይነጠል፤ ማንም ሰው ተጥሎ እንዳይቀር PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Tuesday, 29 December 2009 06:23


ቅ.ኣ.ር.ሊ.ጳ ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትናንትና በቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለነዳያን በሚያዘጋጁት የምሳ ግብዣ ላይ ከ2000 ድኆች ጋር ምሳ በልተዋል። ተጋባዦቹ ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት የመጡ ስደተኞችና ምንም የሌላቸው የሮማ ድኆች ናቸው። ቅዱነታቸው እቦታው በደረሱበት ጊዜ የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር የማኅበሩ መሥራች ፕሮፈሰር ኣንድረያ ሪካርዲ የማኅበሩ ሊቀ መንበር ማርኮ ኢምፓጝልያዞ ከአንድ ሮም ሴትና የሰነጋል ስደተኛ ወጣትና የተርኒ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቪንቸንዞ ፓጝልያ እና ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ልዊጂ ሞረቲ ከድኆቹ አብረው ተቀብለዋቸዋል፣


ፕሮፈሰር አንድረያ ሪካርዲ በእንኳን ደህና መጡ ንግግራቸው፣ “ብፁዕ አባታችን ይህንን ቦታ እንደቤታቸው ከሚቈጥሩት የዚህ ልዩ ኅብረተሰብ ጓደኛ በመሆን ከእኛ አብረው ሲበሉ፣ እርስዎን በቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር ማእድ ከእኛ ጋር ማየት ትልቅ ደስታ ይሰማናል”፣ ሲሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጠው በቦታው በየቀኑ ከአንድ ሺ በላይ እንደሚመገቡ፣ ሰዎቹም በተለያዩ ችግሮች የተጠቁ መሆንቸውን አልደበቁም፣ እንደ ቤተሰብ ሆነው መግብ ብቻ ሳይሆን በፍቅርና በጓደኝነት እንደሚኖሩም ኣብራርተዋል። የድኆች ጓደኛና አለኝታ መሆን ክርስትያንን ያሳድጋል በማለት ትልቁ ጎርጎርዮስ ድኆችን በማገልግል ኃይልና ብርታት እንደሚገኝ ያስተማረውን አስታውሰዋል።


ቅዱስነታቸው ከተለያዩ ኣገሮች ከመጡ ስደተኞች በተለይም በማኅበሩ ብተደራጀ የጣልያነኛ ቋንቋ ትምህርት የሚከታተሉትን ትንሽ ቡድን ሲያነጋገሩ፣ “ቋንቋ በአንድነት ለመኖርና አንድ ቤተ ሰብ ለመሆን የመዋሃሃድ ቍልፍ ነው፣ በቋንቋ ባህልና የባህል ታሪክ እንዲሁም የባህሉ ዕጣ ፈንታ ተደብቆ ይገኛል፣ ይህንን የቋንቋ ትምህርት ዕድል ላበረከተላችሁ የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር አመሰግናለሁ”፣ ሲሉ የተሰጣቸውን ዕድል እንዲጠቀሙበት አደራ ብለው፣ ካበረታቱ በኋላ ማኅበሩ የሠራውን የቤተ ሰቡ የልደት የቤተ ልሔም ግርግም አይተው ምሳ በልተዋል። በምሳ ጊዜ ከቅዱስነታቸው የተለያየ ችግር ያላቸውና ከተለያዩ ወገኖች የመጡ 12 ሰዎች በአንድ ጠረጲዛ ተመግበዋል።


ቅዱስነታቸው እንደ ኢየሱስ ልዩ ጓደኞች የጠርዋቸው የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበረሰብ አብረው በመመገባቸው የተሰማቸውን ደስታና እርካታ ገልጠዋል። ግብረ ሠናዩንም እንዲህ ሲሉ አመጕሰውታል፣ “ኢየሱስን በሚከተሉ የዘመናችን ሓዋርያት በሚደረግ ግብረ ሠናይ እግዚአብሔር በመጀመርያ እንደወደደንና ገናም እንደሚወደን የሚያሳይ እውነት ግልጽ ይሆናል፣ ለዚህም መልስ የምንሰጠው በፍቅር ነው፣ ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና። ይህንን ምግባረ ሠናይ ለማን መሆኑን ለመግለጽ ደግሞ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። እነዚህን ቃላት ስንሰማ ኢየሱን ከሚያመለክቱ ከተቸግሩት ጋር አጋርነት እንድናሳይ አይቀሰቅስምን፣ ጓደኝነትና ኣጋርነት ብቻ ሳይሆን ቤተ ሰብ መሆናችንስ አይሰማንምን” ብለዋል።


ስደትና ችግርን አስመልክተውም፣ የኢየሱስ ቤተሰብም ችግር አጋጥሞታል፣ ገና ቤተሰብ ለመመሥረት ሲጀምሩ በቤተልሔም የሚቀበላቸው አጥተዋል፣ ወደ ግብጽ እንዲሰደዱ ተገደዋል፣ እናንተ የስደትን ችግር ጥሩ ኣርጋችሁ ታውቃላችሁ፣ በችግርና በመከራ ብትገኙም እዚህ እናንተን ለማንከባከብና ለማገልገል የተዘጋጁ የእግዚአብሔር ፍቅር ምልክት የቅዱስ ኤጅድዮ ማኅበር አለላችሁ፣ ዛሬ እዚህ በየቤታችሁ ልታገኙት የምትችሉትን ታገኛላችሁ። ይህ የእውነተኛ ቤተ ሰብ ቤት ነው፣ በቤተሰብ እኔ የሚለው በእኛ ይተካል፣ ማኅበር ይቆማል፣ የፍቅር ማኅበር ስለሆነም እግዚአብሔር ማሃከላችን ይገኛል።


ኢየሱስ የሚሰቃዩትንና ችግር ያላቸውን ሰዎች የሱ ጓደኞች እንደሚያደጋቸውና እንደሚወዳቸው በመረዳት እሱን በመከተል ለሁሉም በተለይም ለተጐዱትና ረዳት ለሌላቸው ለመርዳት ዝግጁነታችን ማረጋገጥ እንድለብን አሳስበዋል፣ “ማንም ሰው ብቻው እንዳይሆን፣ ማንም ሰው እንዳይነጠል፣ ማንም ሰው ተጥሎ እንዳይቀር” ሲሉም አደራ በልዋል።



ቅ.ኣ.ር.ሊ.ጳ ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትናንትና በቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለነዳያን በሚያዘጋጁት የምሳ ግብዣ ላይ ከ2000 ድኆች ጋር ምሳ በልተዋል። ተጋባዦቹ ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት የመጡ ስደተኞችና ምንም የሌላቸው የሮማ ድኆች ናቸው። ቅዱነታቸው እቦታው በደረሱበት ጊዜ የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር የማኅበሩ መሥራች ፕሮፈሰር ኣንድረያ ሪካርዲ የማኅበሩ ሊቀ መንበር ማርኮ ኢምፓጝልያዞ ከአንድ ሮም ሴትና የሰነጋል ስደተኛ ወጣትና የተርኒ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቪንቸንዞ ፓጝልያ እና ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ልዊጂ ሞረቲ ከድኆቹ አብረው ተቀብለዋቸዋል፣
ፕሮፈሰር አንድረያ ሪካርዲ በእንኳን ደህና መጡ ንግግራቸው፣ “ብፁዕ አባታችን ይህንን ቦታ እንደቤታቸው ከሚቈጥሩት የዚህ ልዩ ኅብረተሰብ ጓደኛ በመሆን ከእኛ አብረው ሲበሉ፣ እርስዎን በቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር ማእድ ከእኛ ጋር ማየት ትልቅ ደስታ ይሰማናል”፣ ሲሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጠው በቦታው በየቀኑ ከአንድ ሺ በላይ እንደሚመገቡ፣ ሰዎቹም በተለያዩ ችግሮች የተጠቁ መሆንቸውን አልደበቁም፣ እንደ ቤተሰብ ሆነው መግብ ብቻ ሳይሆን በፍቅርና በጓደኝነት እንደሚኖሩም ኣብራርተዋል። የድኆች ጓደኛና አለኝታ መሆን ክርስትያንን ያሳድጋል በማለት ትልቁ ጎርጎርዮስ ድኆችን በማገልግል ኃይልና ብርታት እንደሚገኝ ያስተማረውን አስታውሰዋል።
ቅዱስነታቸው ከተለያዩ ኣገሮች ከመጡ ስደተኞች በተለይም በማኅበሩ ብተደራጀ የጣልያነኛ ቋንቋ ትምህርት የሚከታተሉትን ትንሽ ቡድን ሲያነጋገሩ፣ “ቋንቋ በአንድነት ለመኖርና አንድ ቤተ ሰብ ለመሆን የመዋሃሃድ ቍልፍ ነው፣ በቋንቋ ባህልና የባህል ታሪክ እንዲሁም የባህሉ ዕጣ ፈንታ ተደብቆ ይገኛል፣ ይህንን የቋንቋ ትምህርት ዕድል ላበረከተላችሁ የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር አመሰግናለሁ”፣ ሲሉ የተሰጣቸውን ዕድል እንዲጠቀሙበት አደራ ብለው፣ ካበረታቱ በኋላ ማኅበሩ የሠራውን የቤተ ሰቡ የልደት የቤተ ልሔም ግርግም አይተው ምሳ በልተዋል። በምሳ ጊዜ ከቅዱስነታቸው የተለያየ ችግር ያላቸውና ከተለያዩ ወገኖች የመጡ 12 ሰዎች በአንድ ጠረጲዛ ተመግበዋል።
ቅዱስነታቸው እንደ ኢየሱስ ልዩ ጓደኞች የጠርዋቸው የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበረሰብ አብረው በመመገባቸው የተሰማቸውን ደስታና እርካታ ገልጠዋል። ግብረ ሠናዩንም እንዲህ ሲሉ አመጕሰውታል፣ “ኢየሱስን በሚከተሉ የዘመናችን ሓዋርያት በሚደረግ ግብረ ሠናይ እግዚአብሔር በመጀመርያ እንደወደደንና ገናም እንደሚወደን የሚያሳይ እውነት ግልጽ ይሆናል፣ ለዚህም መልስ የምንሰጠው በፍቅር ነው፣ ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና። ይህንን ምግባረ ሠናይ ለማን መሆኑን ለመግለጽ ደግሞ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። እነዚህን ቃላት ስንሰማ ኢየሱን ከሚያመለክቱ ከተቸግሩት ጋር አጋርነት እንድናሳይ አይቀሰቅስምን፣ ጓደኝነትና ኣጋርነት ብቻ ሳይሆን ቤተ ሰብ መሆናችንስ አይሰማንምን” ብለዋል።
ስደትና ችግርን አስመልክተውም፣ የኢየሱስ ቤተሰብም ችግር አጋጥሞታል፣ ገና ቤተሰብ ለመመሥረት ሲጀምሩ በቤተልሔም የሚቀበላቸው አጥተዋል፣ ወደ ግብጽ እንዲሰደዱ ተገደዋል፣ እናንተ የስደትን ችግር ጥሩ ኣርጋችሁ ታውቃላችሁ፣ በችግርና በመከራ ብትገኙም እዚህ እናንተን ለማንከባከብና ለማገልገል የተዘጋጁ የእግዚአብሔር ፍቅር ምልክት የቅዱስ ኤጅድዮ ማኅበር አለላችሁ፣ ዛሬ እዚህ በየቤታችሁ ልታገኙት የምትችሉትን ታገኛላችሁ። ይህ የእውነተኛ ቤተ ሰብ ቤት ነው፣ በቤተሰብ እኔ የሚለው በእኛ ይተካል፣ ማኅበር ይቆማል፣ የፍቅር ማኅበር ስለሆነም እግዚአብሔር ማሃከላችን ይገኛል።
ኢየሱስ የሚሰቃዩትንና ችግር ያላቸውን ሰዎች የሱ ጓደኞች እንደሚያደጋቸውና እንደሚወዳቸው በመረዳት እሱን በመከተል ለሁሉም በተለይም ለተጐዱትና ረዳት ለሌላቸው ለመርዳት ዝግጁነታችን ማረጋገጥ እንድለብን አሳስበዋል፣ “ማንም ሰው ብቻው እንዳይሆን፣ ማንም ሰው እንዳይነጠል፣ ማንም ሰው ተጥሎ እንዳይቀር” ሲሉም አደራ በልዋል።
Xmas_Lunchቫቲካን ራድዮ - ቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር የልደት በዓልን ምክንያት የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር በየዓመቱ የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለነዳያን በሚያዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ በመገኘት ቅዱስ አባታችን .ር.ሊ.ጳ ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትላንትና ከ2000 ነዳያን ጋር ምሳ በልተዋል። ተጋባዦቹ ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት የመጡ ስደተኞችና ምንም የሌላቸው በሮማ የሚኖሩ ነዳያን ናቸው። ቅዱነታቸው በስፍራው በደረሱበት ጊዜ የቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር መሥራች ፕሮፈሰር አንድረያ ሪካርዲ፣ የማኅበሩ ሊቀ መንበር ማርኮ ኢምፓግልያዞ፣ የሰኔጋል ስደተኛ ወጣትና የተርኒ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቪንቸንዞ ፓግልያ እና ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ልዊጂ ሞረቲ ከተቀሩት ነዳያን ጋር በመሆን አብረው ተቀብለዋቸዋል፣

ፕሮፈሰር አንድረያ ሪካርዲ በእንኳን ደህና መጡ ንግግራቸው፣ “ብፁዕ አባታችን ይህንን ቦታ እንደቤትዎ በመቁጠርና የዚህ ልዩ ኅብረተሰብ ጓደኛ በመሆን ከእኛ ጋር አብረው በመሳተፍዎና እርስዎን በቅዱስ ኤጂድዮ ማኅበር ማእድ ከእኛ ጋር በማየታችን ትልቅ ደስታ ይሰማናል”፣ ሲሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጠው በቦታው በየቀኑ ከአንድ ሺ በላይ ነዳያን እንደሚመገቡ፣ ሰዎቹም በተለያዩ ችግሮች የተጠቁ መሆንቸውን ገልጠው፣ እንደ ቤተሰብ ሆነው መመገብ ብቻ ሳይሆን በፍቅርና በጓደኝነት እንደሚኖሩም ኣብራርተዋል። የድኆች ጓደኛና አለኝታ መሆን ክርስትያንን ያሳድጋል በማለት ትልቁ ጎርጎርዮስ ነዳያንን በማገልግል ኃይልና ብርታት እንደሚገኝ ያስተማረውንም አስታውሰዋል።

ቅዱስነታቸው ከተለያዩ ኣገሮች ከመጡ ስደተኞች በተለይም በማኅበሩ በተደራጀ...

Last Updated on Sunday, 31 January 2010 21:29
 
በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ የመነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት ሕንድ ትመራለች PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Monday, 14 December 2009 19:54

Mother_Theresa_sisters'_novicesIndependent Catholic News - በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የመነኮሳውያት (የእማሆዮች) የቅርብ ዓመታት ቁጥራዊ ዕድገት ሕንድ ግንባር ቀደሙን ቦታ መያዟ ተገለጠ።

የ"Catholic Culture" ድረ ገጽ ባደረገው አኀዛዊ ዳሰሳ መግለጫ መሠረት ባጠቃላይ ሲታይ እስያና አፍሪካ እ.ኤ.አ. ከ2000 ዓ.ም. ጀምሮ ጥሩ የመነኮሳውያት ቁጥር መጨመር ሲታይ፤ በአውሮፓ፣ አሜሪካና ኦሺኒያ የቁጥር ማቆልቆሉ ታውቋል።

እ.ኤ.አ. ከ2002-2007 ዓ.ም. በእስያ ውስጥ ሕንድ የ9,838 ፣ ቬትናም የ2,545 እንዲሁም ፊሊፒንስና ደቡብ ኮሪያ እያንዳንዳቸው የ500 መነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት አሳይተዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የመነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት ካሳዩት ማኅበራት ውስጥ ሦስት በከራላ (ሕንድ) ውስጥ የተመሠረቱና የብፅዕት እማሆይ የፍቅር ልኡካን እህቶች ላቅ ያለውን ስፍራ ይይዛሉ።

የፍራንቸስካውያት ቅድስት ኪያራ፣ የማርያም ደብረ ቀርሜሎስና የቅዱስ ቁርባን ስግደት መነኮሳይት ማኅበራት በቀጣይነት አባላትን በማግኘት ላይ ናቸው።
ዓለም አቀፍ የመነኮሳውያት ቁጥር ማሽቆልቆል ከሚታይባቸው ማኅበራት መካከል ደግሞ...
Last Updated on Sunday, 31 January 2010 21:26
 
በኢራቅ የአናሳ ሃይማኖቶች ህልውና PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Saturday, 21 November 2009 16:24

ቫቲካን ሬድዮ - በኢራቅ የአናሳ ሃይማኖቶች ህልውና ላደጋ በመጋለጡ ምክንያት ዐቢይ የደኅንነት ጥበቃ እንደሚያስፈልገው የነዚህ አናሳ ሃይማኖቶች ተጠሪዎች የጸጥታ እና የደኅንነት ጥበቃን ጥሪ በማቅረብ በተለይ ደግሞ እ.ኤ.አ. ጥር ወር 2010 ዓ.ም. በአገሪቱ በሚካሄደው ሕዝባዊ መርጫ ወቅት ተገቢ የጸጥታ እና የደኅንነት ዋስትና ያገኙ ዘንድ ለአገሪቱ መንግሥት ጥሪ አስተላልፈዋል።

በኢራቅ አናሳ ሃይማኖቶች ለተለያዩ አደጋዎች በመጋለጣቸው ምክንያት መፍትሔው ራስን ለማዳን አገር ጥሎ መሰደድ ብቻ በመሆኑ የተያያዙት ስደት እንዲወገድ ከመንግሥት የጸጥታ እና የደህንነት ዋስትና መረጋገጥ ይኖርበታል። በኢራቅ አናሳ ከሚባሉት ሃይማኖቶች ውስጥ የእስልምና እና የክርስትናን አንዳንድ የእምነት ሥርዓቶችና ትምህርተ ሃይማኖትን በአንድ በማቀላቀል የሚያስተምር 300 ሺሕ ኢራቃውያን የሚከተሉት የሻባክ ሃይማኖት አንዱ ሲሆን፣ ሌላው የያዚዲ ሃይማኖት፣ የከለዳያን ሥርዓት የምትከተል ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን፣ የኦርቶዶስክ፣ የአሲሪያ፣ የአርመን፣ የአንግሊካን አቢያተ ክርስትያን የሚመለከት ጉዳይ ሲሆን፣ በኢራቅ በመንግሥት ደረጃ ሳይሆን በአቋም ስነ ሓሳብ የተደገፈ ጸረ የአናሳ ሃይማኖት ተግባር እየተስፋፋ መሆኑ ይነገራል።

Last Updated on Sunday, 31 January 2010 21:26
 
እርቅን፣ ፍትሕ እና ሰላምን ተግባራዊ ለማድረግ ንጹሕ ልብ፣ አዲስ አመለካከትና ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት PDF Print E-mail
Written by Administrator   
Monday, 26 October 2009 15:23
ቫቲካን ሬድዮ - ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛ በተገኙበት እዚህ በቫቲካን እ.ኤ.አ. ከጥቅምት 4 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሄድ የሰነበተው አፍሪቃ የራሷ ዕጣ ፈንታ ግንባር ቀደም ተዋናይ እና ባለ ቤት ትሆን ዘንድ ያሳሰበው ይፋዊው ሁለተኛው የአፍሪቃ ብፁዓን ጳጳሳት ሲኖዶስ መጠናቀቁ ሲገለጥ፣ ቅዱስነታቸው ቅዳሜ ዕለት በተዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ ተገኝተው ለብፁዓን የሲኖዶስ አበው ባሰሙት ንግግር፣ ብፁዓን የሲኖዶስ አበው ያካሄዱት ሲኖዶስ የሚመሰገን እና የተዋጣለት እንደነበረ ገልጠው፣ ይህ እርቅ ፍትሕ እና ሰላም በሚል ጠቅላይ ርእስ ተመርቶ የተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪቃ ብፁዓን ጳጳሳት ሲኖዶስ፣ እንዲከናወን ለፈቀደው በመንፈስ ቅዱስ ድጋፍ ቃሉን እና ፈቃዱን በማዳመጥ ወደ ውህደት በሚመራው መንገድ ለመጓዝ እንድንችል ላደረገው አስጀምሮ ላስጨረሰን እግዚአብሔር ምስጋና ይገባዋል ካሉ በኋላ፣
Last Updated on Friday, 05 February 2010 20:27
 
<< Start < Prev 1 2 3 4 5 6 7 8 Next > End >>

Page 1 of 8

የሳምንቱ መልእክት

"እግዚአብሔርን ስናፈቅር አይሁን እንጂ በተቀረው ነገር ሁሉ ሚዛኑን የጠበቀ አካሄድ ጥሩ ነገር ነው።" ቅዱስ ፍራንሲስ ዘሳሌስ

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች

በአሁኑ ሰዓት ጎብኚዎች:

We have 150 guests online

Copyright © 2008 -2009 Cistercian Monks in Ethiopia - Ethiopian Catholic Church

joomla 1.5 statistics