ሲታውያን መነኮሳን በኢትዮጵያ

Cistercian Monks in Ethiopia - እንኳን ደህና መጡ!
እኛ ማነን...

 (if you can't read our Amharic pages, please download the font here: Visual GeezUnicode)


ቅዱስ ቁርባን ኢየሱስ ክርስቶስን ይሰጠናል!

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን በመከተል የሲታዊ መንፈሳዊነትን መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን እግዚአብሔርን በግላዊና ማኅበራዊ ጸሎት በቀጣይነት የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል። ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን። 1ጴጥ.4:11 

  

የብጹዕ ገብረ ሚካኤል አጭር ሰማዕታዊ ገድል 

ብጹዕ ገ/ሚካኤል በ 1788 በጎጃም ልዩ ስሙ ዲቦ በተባለ አውራጃ ተወለዱ። ከልጅነታቸው ጀምረው የአገራችንን ትምህርት ማለትም ዜማ፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ቅኔ ወዘተ. . . ለመማር ተሰማሩ። በትምህርት ትጋታቸውና በውጤታቸው መምህሮቻቸው በጣም አደነቁዋቸው። ይህን ሁሉ መንፈሳዊ እውቀት ካካበቱ በኋላ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር በሙሉ ልባቸው ሊሰጡ ፍላጎት ዕቅድ ስለነበራቸው በ25 ዓመታቸው በመርጡለ ማርያም ገዳም ገቡ። በጣም ጎበዝና ከፍተኛ የዕውቀትና የእውነት ጥማት ስለነበራቸው ከገዳም ወደ ገዳም ይዘዋወሩ ነበር። እንደዚህም እያሉ ሲታገሉ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ሕሊናቸውን ያስጨንቅ የነበረው የሃይማኖት ልዩነትና ጭቅጭቅ ገጠማቸው። 

በዚህም ዕረፍት አጥተው ተጨንቀው "ጌታዬና መድኃኒቴ፡ ጽድቅ የት እንደምትገኝ ግለጥልኝ፡ አንተ ጻድቅ እንደሆንክ አምናለሁ። ጻድቅ ነኝ፤ ትክክለኛው የኔ ነው ወዘተ . . . የሚሉኝ ብዙዎች ናቸው፤ እኔ ግን ጽድቅን ሳትበላሽ ከምንጭዋ ላገኛት እፈለጋለሁ" እያሉ ጸለዩ። እግዚአብሔርም ጸሎታቸውንና የልባቸውን ምኞት ሰምቶ ከቅዱስ ኣቡነ ያዕቆብ ጋር አገናኛቸው። ብጹዕ ገ/ሚካኤል በቅዱስ አቡነ ያዕቆብ ሕይወት ዘመን በብዙ የሃይማኖት ትምህርት ታነጹ። 

በ 1851? በሀገሪቱ ፓትርያርክ ስላልነበር በደጃች ውቤ ተመርጠው ወደ እስክንድርያ ፓትርያርክ እንዲሰጣቸው ሊጠይቁ መልእክተኛ ሆነው ወደ አሌክሳንድርያ ተላኩ :: ከመልእክተኞቹ አንዱ ደግሞ በዛን ግዜ ጥሩ ዝናና ተቀባይነት የነበራቸው ካቶሊካዊው አባ ያዕቆብ (አሁን ቅዱስ አቡነ ያዕቆብ ) አንዱ ነበሩ :: በዚህ አጋጣሚ ስለሃይማኖታቸው ለመወያየት ጥሩ አጋጣሚ አገኙ :: አባ ያዕቆብ ለሚያቀርቡላቸው ለነበረው <ክርስቶስን > በሚመለከት በደንብ ያውቁ ስለነበረ፤ እነሱን ለማስረዳት የሰጡት መልስ <ስለ ሥላሴ በምታስተምሩት ትምህርት ላይ: አንድ አምላክ ሦስት አካላት ትላላችሁ:: ታዲያ የኢየሱስ አንድ አካል ሁለት ባሕሪ እንዴት ሊከብዳችሁ ቻለ?> እንደዚህ እየተጠያየቁ: አንዱ ከአንዱ እየተማረ ከእስክንድርያ ወደ ቤተልሔም: ቅ .ጴጥሮስ ንግደት በአንድ ላይ ፈጸሙ :: 


ከ1846-1854 ካቶሊክ ስለሆኑና በፓትርያርክ አቡነ ሰላማ ትእዛዝ በተለያየ ጊዜ ወደ እስር ቤት ወረዱ:: በእስር ቤት ውስጥ በጣም በሚያሰቅቅ ሁኔታ በዱላ ተደበደቡ:: ምንም ለውጥ ስላላሰዩና በእምነታቸው ጸንተው ስለተገኙ እንደገና ለማረጋገጥ ብለው አቡነ ሰላማ: አባ ገ/ሚካኤልን ከእስር ቤት አስጠርተው ስለእምነታቸው ጠየቁዋቸው:: ምንም ለውጥ ስላላገኙባቸው ወደ ንጉሡ (አጼ ቴዎድሮስ) አሳልፈው ሰጡዋቸው:: ንጉሡም በግርፋት እንዲቀጡ አዘዙ:: አሁንም ከእምነታቸው ነቅነቅ ስላላሉ ንጉሡ ወታደሮቹን ሁላችሁም በአንድ ጊዜ ግረፉዋቸው ሲሉ አዘዙ:: 150 ጅራፍ ፊታቸው ላይ ተገረፉ (ያቺ የቀረችውን አንድ ዓይናቸውን ሊያጠፉ):: በዛ የነበሩ ስቃያቸውን የሚመለከቱ የነበሩ ሲመሰክሩ <የገራፊዎቹን ብዛት : የግርፊያውን ቁጥር : ይህን ያህል ተብሎ መናገር አይቻልም > በማለት የግርፊያውን አሰቃቂነት ይገልጻሉ:: በዛ የነበሩ ሰዎች በቃ <ሞተዋል >: እያሉ እየተነጋገሩ እያሉ : ሰማዕቱ (አባ ገ/ሚካኤል ) ከዛ ሁሉ ድብደባና ግርፊያ በኋላ : ምንም እንዳልሆኑ፡ ፊታቸው ላይ ቁስል የምትባል ሳትታይባቸው : አይናቸው ከበፊቱ የበለጠ ብሩሕና ደስተኛ ሆነው ወደ እስር ቤት ሲያመሩ አይዋቸው። ከሁለት ቀን በኋላ በንጉሡ ትእዛዝ መሠረት በሰንሰለት ታስረው ከወታደሮች ጋር በእግር እንዲጓዙ ተደረገ :; በዚህን ጊዜ ዕድሜያቸው ከ 60 በላይ ነበር:: ይህንን ስቃያቸውን የተመለከቱ ወታደሮች በጣም ከመገረምና ከመደነቅ የተነሳ አባ ገ/ሚካኤልን <ቅዱስ ጊዮርጊስ > በሚል ቅጽል ስም ይጠሯቸው ጀመር:: ምክንያቱም ቅ .ጊዮርጊስ 7 ጊዜ ሞቶ ተነሳ የሚባል ታሪክ ስላለ:: እንደገና ንጉሡ አጼ ቴዎድሮስ እና አቡነ ሰላማ በተገኙበት እንደገና አባ ገ/ሚካኤልን ስለእምነታቸው ጠየቁዋቸው:: አባ ገ/ሚካኤልም "አምባገነኑና እውነተኛው የክርስቶስ ጠላት ሆይ ስማ! ዛሬ በር.ሊ.ጳ. ፒዮ 9ኛ በምትመራውና በምታስተምረው ካቶሊክ ቤ/ያንና: እኔ የእምነት ልጁ - እስከመጨረሻው የሕይወት እስትንፋሴ ድረስ - ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው በሆነው ክርስቶስ አምናለሁ - ደግሞም መሞት የምፈልገው በዚህ እምነት ነው " ሲሉ መሰከሩ :: በዚህ ምስክርነታቸው ደግሞ ሞት ተፈረደባቸው: :: ነሐሴ 23 ደግሞ ስለ ካቶሊካዊ እምነታቸው ብለው በሰማዕትነት ሕይወታቸውን ኣሳልፈው ሰጡ ::

ጥቅምት 3/1926 እ.ኤ.አ. በቅዱስ ጴጥሮስ ቤ/ያን በተደረገው መስዋዕተ ቅዳሴ ብጽዕነታቸው ታወጀ:: የኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ካህናት አርአያና ባልደረባ (patron) ይባላሉ ።

ሰላም ለሞትከ ዕረፍተ ጻድቃን ዘኮነ : 

አምሳሊሁ ለኢየሱስ ዘሞተ በእንቲአነ : 

ለነኒ ሀበነ ገ/ሚካኤል አቡነ 

ለነፍስነ ሞገስ ወለልብነ ዛህነ 

ወኅሉቀ ንርከብ ዘነፍስነ ድኂነ ::

የጻድቃን እረፍት ለሚመስለው ሞትህ ሰላም ይሁን፡አባታችን ገ/ሚካኤል ሆይ ! ሞትህ ስለ እኛ የሞተውን የክርስቶስን ይመስላል፡አባታችን ሆይ ለነፍሳችን ድኅነት እንድናገኝ ለልባችን ጸጋና እረፍት ስጠን።

የሀገራችን ቅዱስ : ስለ ሀይማኖታቸው ብለው በመስዋዕትነት የሞቱት የብጹዕ ገብረሚካኤል በዓል ነሐሴ 23 ይከበራል :: 

ዋዜማው <ተሰአሎ ንጉሥ ለብጹዕ ገብረሚካኤል : ወይቤሎ ንግር ሃይማኖተከ : አውሥኦ ብጹዕ አአምን በኢየሱስ አምላክ ወሰብእ : ወበአሐቲ መንበረ ጴጥሮስ : ሰማዕተ ኮነ በሃይማኖት ወወረሰ መንግሥተ ሰማያት > እየተባለ ይከበራል ;; 

ትርጉሙ : <ንጉሡ (አጼ ቴዎድሮስ) ብጹዕ ገብረሚካኤልን ሀይማኖትህን (እምነትህን) ተናገር ብለው ጠየቁት : ብጹዑም አምላክና ሰው በሆነው ኢየሱስና በአንዲት መንበረ ጴጥሮስ አምናለሁ ብሎ ተናገረ : በሰማዕትነት ሞተ : በእምነታቸው ደግሞ መንግሥተሰማይን ወረሱ >

አባ ጸሊ በእንቲአነ : እስመ ጸሎተ ጻድቅ ይሰምዕ እግዚአብሔር


 

  

 
መሃይምነትን በማጥፋት ክርስቶሳዊ እውነትን መመስከር PDF Print E-mail
  
Thursday, 02 July 2009 23:47

ኦፓም በመባል የሚጠራው ከዓለማችን መሃይምነትን በማጥፋት ተልእኮ አገልግሎት የሚሰጠው እ.ኤ.አ. በ 2006 ዓ.ም. የተቋቋመው ብፁዓን ጳጳሳት ካህናት ገዳማውያን እና ዓለማውያን ምእመናንን ያካተተው የወንድማማችነት ልኡካን በሚል መጠሪያ የሚታወቀው ማኅበር በሚሰጠው አገልግሎት አማካኝነት የእግዚአብሔርን ፍቅር የሚመሰክር መሆኑን የማኅበሩ ሊቀ መንበር ብፁዕ አቡነ አልዶ ማርቲኒ ገለጹ። 

Last Updated ( Friday, 03 July 2009 00:13 )
 
ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም እንዲሰፍን በድጋሚ አሳሰቡ PDF Print E-mail
  
Friday, 26 June 2009 22:11

(ሬድዮ ቫቲካን) - 2009-06-27 - ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ አሥራ ስድስተኛ ትናንትና ረፋድ ላይ በአኅጽሮተ ቃል ሮአኮ በመባል የሚጠራው የምሥራቅ አብያተክርስቲያናት ተራድኦ ማኅበር አባላትን ተቀብለው አነጋገሩ። 

ቅዱስ አባታችን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ በዚሁ ግኑኝነት እንደገለጹት የመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ በእጅጉ እንደሚያሳስባቸው ጠቅሰው የቅድስት ሀገረ ጳለስጢና ቤተክርስቲያን ከእስራኤል ፍሊስጤም ግጭት የተሳሰረ መሆኑ ማመልከታቸው ተገልጠዋል።

የመካከለኛው ምስራቅ ታሪካዊ እና አሳዛኝ ግጭት መቀረፍ የሰላም እምነ መሠረት መሆኑ ያሰመሩበት ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ ፡ በአሁኑ ወቅት ጋዛ ሰርጥ ከሁሉም በመገለል ህዝብዋ ለችግር መጋለጡ አመልክተዋል። 

Last Updated ( Wednesday, 01 July 2009 09:45 )
 
የክህነት ዓመት ዛሬ በይፋ ተጀመረ PDF Print E-mail
  
Saturday, 20 June 2009 08:51
ቅዱስ ዮሐንስ ቪየን - የአርስ ቆሞስ
ቫቲካን ራድዮ - 2009-06-20- ባለፉት ዝግጅቶታችን እንዳመለከትነው የካህናት ዓመት ዛሬ በጸሎተ ሠርክ ዘጥቀ ቅዱስ ልበ ኢየሱስ በይፋ ተጀመረ። ይህ እ.አ.አ ከዛሬ ሰኔ 19 ቀን ጀምሮ እስከሚመጣው ሰኔ 19 2010 ዓ.ም. የሚቆይ የጸሎት የአስተንትኖና የመታደስ ጊዜ በመሆን ካህናት ለዛሬው ዓለም ሕያው የወንጌል ምሥስክርነት እንዲሰጡ የሚቀሰቅስ ነው።

ለዚህ የክህነት ዓመት ማወጅ ምክንያት የሆነው በትሕትናው እና በቅድስናው የካህናት ኣብነት የቅዱስ ዮሓንስ ቫያነይ የዕረፍት 150ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ነው። የቅዱስ ዮሓንስ ቫያነይ ሕይወትና የክህነት ጥሪ ልክ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች በጻፈው ኣንደኛ መልእክቱ ምዕራፍ ኣንድ ላይ “እግዚአብሔር ጥበበኞችን ለማሳፈር በዓለም እንድ ሞኞች የሚቈጠሩትን ሰዎች መረጠ፣ ብርቱዎችንም ለማሳፈር በዓለም እንደ ደካሞች የሚቈጠሩትን መረጠ፣ በዓለም ሰዎች ዘንድ ክቡር ሆኖ የሚታየውን ነገር ለማጥፋት በዓለም የተዋረደና የተናቀ ከንቱም መስሎ የሚታየውን ነገር መረጠ።” እንደሚለው ነው። በጊዜው በነበሩት ሰዎች ሚዛን ቅዱስ ዮሓንስ ቫያነይ ለምንም ብቃት የሌለው ተብሎ የተገመተ ብዙ የተጋለ የእግዚአብሔር ሰው ነበር፣ ሆኖም ግን እግዚአብሔር መሣርያው እንዲሆን ስለመረጠው ለክህነት አዲስ ትርጉም ሰጠው፣ ክህነት የጥቀ ቅዱስ ልበ ኢየሱስ ፍቅር ነው በማለት ሌት ተቀን በቅዱስ ቍርባን ፊት ተደፍቶ በመጸለይ በአብነቱ ብዙ ሰዎች ወደ ጌታ እንዳቀረበና ከጊዜው ከነበሩ ካህናት የበለጠ እረኛ ከመሆን አልፎ የዓለም ሙሉ የካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን ቆሞሶች ጠበቃ ሆነዋል።

Last Updated ( Wednesday, 01 July 2009 09:49 )
 
ዓመተ ሐዋርያ ጳውሎስ በርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ የመዝግያ ሥርዓት ተፈጸመ፡ PDF Print E-mail
  
Tuesday, 30 June 2009 12:35

 (ሬድዮ ቫቲካን) 2009-06-30 - ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ አሥራ ስድስተኛ ትናትና ከቀትር በኃላ ከቅድስት መንበር ቅጥር ውጭ በሚገኘው የቅዱስ ጳውሎስ ካተድራል ተገኝተው በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት የዓመተ ጳውሎስ መዝግያ ሥርዓተ ሰርክን መሩ። 

የቁስጢንጢንያ ቤተክርስትያን ፓትርያርክ የብፁዕ ውቅዱስ ባርቶለመዮ አንደኛ ልዑካንም በዚሁ ሥርዓት መገኘታቸው ታውቋል። 

በዚሁ ለአንድ ዓመት የዘለቀው ጳውሎሳዊ ዓመት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ምእመናን ካተድራሉን መጐብኘታቸውም ተገልጿል ።

ቅዱስ አባትቻን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ ትናትና ከቀትር በኃላ የጳውሎሳዊ ዓመት መዝግያ ሥርዓት ሲፈጽሙ እንደገለጡት ፡ ካተድራሉ ውስጥ ለዘመናት በታቀበው መቃብር የተካሄደው የሳይንሳዊ ጥናት ግኝት የቅዱስ ጳውሎስ ቅሪት መሆኑን ያረጋገጠ ይመስላል ብለዋል።

Last Updated ( Wednesday, 01 July 2009 09:48 )
 
ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን ካህናት ያስፈልጓታል PDF Print E-mail
  
Wednesday, 24 June 2009 16:38

(ቫቲካን ሬድዮ)-2009-06-24- ቅ.ኣ.ር.ሊ.ጳ በነዲክቶስ 16 በዓመተ ክህነት መክፈቻ ላይ ባሰሙት ስብከት የክርስቶስ አካል ለሆነችው ቤተ ክርስትያን እውነተኛ እረኞች ያልሆኑና የበጎች ሌቦች ከሆኑ የካህናቶችዋ ክፍል ኃጢኣት በላይ የሚያሳዝናትና የሚያሳቃያት ምንም የለም። የዓመተ ክህነቱ ርእሰ ጉዳይ የክርስቶስ ታማኝነት የካህናት ታምኝነት ነው፣ ይህም ክርስቶስ ለአባቱ እስከ ሞት ታማኝና ታዛዥ ሆኖ በመሥዋዕቱ ዓለምን እንደአዳነ ሁሉ ቤተ ክርስትያንም ምእመናንን የእግዚአብሔር ምሕረት ፍቅር ቀምሰው እስከመመሥከር የሚረድዋቸው እረኞች ቅዱሳን ካህናት ያስፈልግዋታል።...

Last Updated ( Wednesday, 01 July 2009 09:46 )
 
በሃማኖቶች መካከል በመደረግ ላይ ያለው ግኑኝነት PDF Print E-mail
  
Wednesday, 17 June 2009 22:04

 በካቶሊክ እና በሂንዱ ሃይማኖት መካከል ለሚካሄደው ግኑኝነት አንድ አዲስ ምዕራፍ መከፈቱ ከተለያዩ ሃይማኖቶች ጋር የሚካሄደውን ግኑኝነት የሚከታተለው ጳጳሳዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር ብፁዕ ካርዲናል ዣን ልዊ ቱራን በህንድ ሓዋርያዊ ጉብኝት ፈጽመው በተመለሱበት ወቅት ይፋ ማድረጋቸው ተገለጠ።

ብፁዕ ካርዲናል ቱራን በህንድ ኦሪሳ ክልል አክራሪያን የሂንዱ ሃይማኖት ምእመናን ጸረ ክርስትያን አመጽ ከማነሳሳታቸው ቀደም ብሎ እ.ኤ.አ. ባለፈው 2008 ዓ.ም. ሓዋርያዊ ጉብኝት አካሂደው እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ የሂንዱ አክራሪያን ጸረ ክርስትያን አመጽ መሠረታዊው ምክንያት ለይቶ ለማወቅ ብፁዕ ካርዲናል ታውራን የሂንዱና የካቶሊክ ሃይማኖት ዓበይት መንፈሳዊ መሪዎች ጋር በመገናኘት ሀሳብ ለሀሳብ እንዲለዋወጡ ያቀረቡት ጥሪ እ.ኤ.አ. ባለፈው ሰኔ 12 ቀን 2009 ዓ.ም. በህንድ ቦምበይ ከተማ ዝግ በሆነ ጉባኤ እውን መሆኑ ተገልጠዋል። 

Last Updated ( Wednesday, 01 July 2009 09:49 )
 
<< Start < Prev 1 2 3 4 Next > End >>

Page 1 of 4

ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ላይ በ1973 ዓ.ም. የግድያ ሙከራ ያደረገው ቱርካዊ ከማረምያ ቤት በቅርቡ ሲወጣ በመንበረ ጴጥሮስ - ቫቲካን - መጠመቅ እንደሚፈልግ ገለጸ...ይመልከቱ


Get the Flash Player to see this player.

የሳምንቱ መልእክት

"በሕይወታችን ከሚይዙን ፍቅሮች ሁሉ የላቀ ፍቅር የሚይዘን ከእግዚአብሔር ጋር ስንፋቀር ነው። ወደር የለሽ ፍለጋም እሱን ለማግኘት የምናደርገው አሰሳ ነው፤ እንዲሁም ትልቁ ስኬታችን ሊሆን የሚችለውም እሱን ማግኘት ስንችል ብቻ ነው!" ቅዱስ አውጎስጢኖስ

የተለያዩ

ርእሶቹን በመጫን መጎብኘት ይችላሉ:
በአዲስ መልክ የተዘጋጀው የቫቲካን አማርኛና ትግርኛ ድረ-ገጽ
በቫቲካን ሬድዮ የሚተላለፉትን ዜናዎች ለማንበብ በአዲስ መልክ የተዘጋጀውን የቫቲካን (መንበረ ጴጥሮስ)አማርኛና ትግርኛ ድረ-ገጽ ይጎብኙ
A must see video music!
"Give this hope to all the people" በማለት ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ያበረታቱት ወጣት አካል ጉዳተኛ ቪዴዮ
የተለያዩ የመዝሙር ቪዲዮዎች
የተለያዩ አማርኛና እንግሊዘኛ የመዝሙር ቪዲዮዎች።
የካቶሊካዊት ቤ/ያን አማርኛ መዝሙሮች
ከ70 በላይ የሚሆኑ አማርኛ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መዝሙሮችን ማዳመጥ ይችላሉ።

ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ

  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ
  • ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን - አዲስ አበባ

በአሁኑ ሰዓት የጎብኚዎች ብዛት:

We have 3 guests online
Copyright © 2009 Cistercian Monks in Ethiopia. All rights reserved.
var sc_project=4008807; var sc_invisible=0; var sc_partition=48; var sc_click_stat=1; var sc_security="7ceee833";
joomla 1.5 statistics