እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ክፍል 2 - አእምሮ ወደ እውነት ልብም ወደ ደስታ ይመጥቃል!

አእምሮ ወደ እውነት ልብም ወደ ደስታ ይመጥቃል!

አጎስጢኖስ በዚህ ዓይነቱ ሥርዓት አልባ ኑሮ ሲኖር በውስጡ ግን የሰላምና የኅሊና እርጋታ እጦት የሚያጠቃው የመንፈስ መታወክና ያለመደሰት ስሜት እንደነበረው ራሱ የሚያምነው ነገር ነው። በዚህ ወቅት በሥጋዊ ፍትወትና በጊዜያዊ ነገሮች ተሸንፎ ነበር። ቀጥሎ ግን የእምሮን ብርሃን ለማግኘት ወይም ደግሞ ዕረፍት ያጣች ነፍሱ እንድትረጋጋለት በመመኘት ወደ ፍልስፍና አዘበለ። ምንም እንኳ ዕረፍትን፣ ደስታንና የተመኘውን የአእምሮ ብርሃን ባያገኝም በጊዜው ያስደነቁ የጥበብና የእውቀት መጻሕፍትን በመመርመሩ አስተያየቱና አስተሳሰቡ ዳበረ። በተለይም ሲሰሮ (ቺቸሮኔ) የሚባል ሮማዊ የደረሰው "ሆርተንስዮስ" የሚል መጽሐፍን ባነበበ ጊዜ ይበልጥ ለማወቅና እውነትን ለመጨበጥ የነበረው የማይገታ ምኞትና ጉጉት በውስጡ ተቀጣጠለ። ይህ መጽሐፍ ያሳደረበትን ስሜት ራሱ ሲገልጽ "የዚህ ዓለም አላፊና ቀሪ እውቀት ዋጋ የሌለው መሆኑን ተገነዘብሁ፤ ስለዚህም ዘለዓለማዊት የሆነች ጥበብን ለማቀፍ የማይገታ ፍላጎት አደረብኝ፤ ልቤም ቢሆን ምድራዊና አላፊ የሆነውን ነገር በመናቁ አምላክን ለመፈለግ ብርቱ ናፍቆት ተሰማኝ..." ይላል።

የሰው ልጅ አእምሮ እውነትን ለማግኘት በብርቱ ግለት እንደሚወናጨፍ ጥይት ነው። አውጎስጢኖስም የሚናፍቅትን እውነት ለማግኘት በብርቱ ጣረ። ነገር ግን ይህ የዓለምና የሰው ልጅ ፍልስፍና በልቡ የተቀጣጠለውን የእውነት ፍለጋ ግለቱን ሊያበርድለትና ሊያረካለት የማይችል መሆኑን ተገንዘብ። አሁንም ሊያገኛትና የሕይወቱ ፍልስፍና መመሪያን ሊቀዳባት የተመኛት እውነትን "ላገኛት እችል ይሆን" በሚል ሃሳብ መንገዱን ለውቶ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ ሊፈልጋት ተነሣ።

ቅዱሳት መጽሐፍትን በዓለማዊ አመለካከት በተመለከታቸው ጊዜ በዘመኑ ገኖ እንደነበረው እንደ ፍልስፍናና እንደ እውቀት መጽሐፍት ጥልቅና ረቂቅ ትምህርትን አላገኘባቸውም። በሥጋዊና በሰብአዊ ዓይን ስለተመለከታቸውና ስላገባው ምንም እንኳ ሕይወቱ ከቅዱስ መጽሐፍ ትምህርት ጋር የማይጣጣምና በስሕተት ላይ ያለ መሆኑን ቢያውቀውም ሕይወቱን በቃለ እግዚአብሔር መንፈስ መመልከትና ጥልቅ ኃጢአቱን አምኖ መቀበል ተሳነው። በዚህና ይህን በምሳሰለው ምክንያት ቅዱስ መጽሐፍንም ቢሆን እንደማይጠቅም ቆጥሮ ወደ ጎን ተወው። እውነትን ለማግኘት ባደረገው ያልተቋረጠ ጥረት አሁንም ሳይሰለች ሲዳስስ ከአረምኔነት ጋር ወደ ተለወሰ ወደ ማኒ ትምህርት (የማኒኬይዝም ትምህርት) መውደቅ ግድ ሆነበት።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት