እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የሃንጋሪዋ ቅድስት ኤልሣቤጥ

የሃንጋሪዋ ቅድስት ኤልሣቤጥ

የሃንጋሪዋ ቅድስት ኤልሣቤጥኤልሣቤጥ እ.ኤአ. 1207 ዓ.ም. የተወለደች የሃንጋሪው ንጉሥ አንድርያስ ልጅ ናት፡፡ ገና በወጣትነቷ የቱሪንግያውን ባላባት ሎድዊግን አግብታ ሦስት ልጆች ወለደች፡፡ በጸሎት ትተጋ ነበረ፣ ባሏ ከሞተባት በኋላም ሃብቷን ሁሉ ትታ ለበሽተኞች ባሠራቸው ሆስፒታል ውስጥ እነሱን መንከባከብ ጀመረች፡፡ ... 1231 ዓ.ም. ማልበርግ ውስጥ አረፈች፡፡

የቅድስት ኤልሳቤጥ ነፍስ አባት ከነበረው ከማርበርጉ ኮንራድ ደብዳቤ የተወሰደ ንባብ

ኤልሣቤጥ ክርስቶስን በድሆች ውስጥ አየች፣ ወደደቻቸውም”

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የኤልሣቤጥ ቅድስና ሙሉ እየሆነ ሄደ፡፡ ሕይወቷን በሙሉ የድሆች መጽናኛ ነበረች፤ አሁን የረሃብተኞች ረዳት ሆነች፡፡ ከታላላቅ የግንብ ቤቶቿ ከአንድ ደጃፍ የእንግዳ ማረፊያ አሠርታ በልዩ ልዩ በሽታዎች ይሰቃዩ የነበሩትን ወንዶችና ሴቶች በዚያ አሳረፈች፡፡ ወደዚህም ቦታ ሌላ ምጽዋት ለመቀበል የመጣ ማንም ሰው ከርስዋ ያልተቆጠበ እርዳታ ያገኝ ነበር፡፡ የባልዋ ግዛት በሆነው ሁሉ ያላትን ንብረት ሁሉ በመጠቀም፣ በመጨረሻም ጌጦቿንና ልብሶቿንም ሁሉ እየሸጠች በርሱ ግዛት ውስጥ ላሉት ሁሉ ትረዳ ነበር፡፡

በሽተኞቹን በቀን ሁለት ጊዜ፣ ጠዋት በማለዳና  ፀሐይ ሳትጠልቅ ሄዳ ትጐበኛቸው ነበር፣ ከነዚህም በሽተኞች ውስጥ ስቃይ የሚበዛባቸውን ራሷ ትንከባከባቸው ነበር፡፡ እርሷ ታበላቸው፣ አልጋቸውን ትጠርግ፣ ትሸከማቸውና በፈለጉት መንገድ ትንከባከባቸው ነበር፡፡ ባልዋም መልካም ሰው ስለ ነበር በምታደርገው ሁሉ ይስማማ ነበር፡፡ እርሱ ሲሞት ፍጽምናን ለማግኘት መጣጣር አለብኝ ብላ አሰበች፡፡ ወደኔም መጥታ ከቤት ወደ ቤት እየዞረች ለመለመን እንድፈቅድላት እያለቀሰች ለመነችኝ፡፡ በዚያ ዓመት ዓርብ ስቅለት፣ የቤተ-ክርስቲያን አልባሳትና ጌጦች ከተነሡ በኋላ በቤተ-ክርስቲያኑ መሰዊያ ፊት ለፊት ተንበርክካ እጆቿን አሳረፈች፡፡ ከዚያም የቤተ-ክርስቲያኑ ካህናት በተሰበሰቡበት ምድራዊ ሃብቷንና መድኃኒታችን በወንጌል ውስጥ እንድንሰጥ የሚመክረንን ሁሉ በፈቃዷ ተወች፡፡

 

ይህን መሃላ ከፈጸመች በኋላ እንኳን ባሏ በሕይወት ዘመኑ ከነበረበት ጊዜ ትኖርበት በነበረው ሁኔታና በአስተዳደር ሥራዎች ውስጥ እንዳለች ተረዳች፡፡ ከዚያም ያለኔ ፈቃድ ወደ ማርበርግ ተከትላኝ በመምጣት በከተማው ውስጥ የድኩማን ማረፊያ በመሥራት በሽተኞችንና አካል ጉዳተኞችን በዚያ ሰበሰበች፣ ከዝቅተኞቹና ከምስኪኖቹም ጋር በአንድ ማዕድ ቀረበች፡፡ ነገር ግን ይህ ሁሉ ውጫዊ ተግባሯ ነበር፡፡ ይህን ከእግዚአብሔር ፊት እናገራለሁ፤ ከዚህች የበለጠ ስለ እግዚአብሔር የምታስብ ሴት አይቼ አላውቅም፡፡ የግል ጸሎቷን ለማድረግ ስትመጣ አንዳንድ ቄሶችና ደናግል ብዙ ጊዜ ያይዋት ነበር፣ ፊቷ ወደ ብርሃን ተለውጦ  ፀሐይም ከዓይኖኟ የምታበራ ይመስል ነበር፡፡ ከመሞቷ በፊት ኑዛዜዋን ሰማሁ፡፡ ሃብቷንና ልብሶቿን ምን እንደሚሆኑ ስጠይቅ የቀራት ማንኛውም ነገር የድሆች እንደሆነ ገልጻ ለብሳው ለመቀበር  ሰበችው አሮጌ ቀሚስ በስተቀር ሁሉንም ለድሆች እንዳከፋፍል ነገረችኝ፡፡ ከዚያም ቅዱስ ቁርባንን ተቀበለች፡፡ ከዚህ በኋላ የምሽት ጸሎት ሰዓት እስኪደርስ ድረስ በስብከት ስለሰማቻቸው ቅዱሳን ነገሮች ተናገረች፡፡ ይህን ስትጨርስ በአጠገቧ ለሚገኙት ሁሉ ከጸለየች በኋላ እንቅልፍ ያሸለባት መስላ አረፈች፡፡ በዓሏም ኅዳር 8 ቀን ይከበራል።

የሃንጋሪዋ ቅድስት ኤልሣቤጥ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት