እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ቅድስት ዮሴፋዊት ባኪታ /1869-1947/

ቅድስት ዮሴፋዊት ባኪታ /1869-1947/

Bakhita

Bakhita Kwashe-big

"ዓለም ገና ክርስቶስን አታውቅምና ሥጋዬን ሁሉ በጣጥሼ እስከ ምድር ዳርቻ በመዝራት ጌታ ኢየሱስን በሕይወቴ እሰብካለሁ" ቅድስት ባኪታ

የዚህች አስገራሚ ሱዳናዊት ወጣት የሕይወት ጉዞ፣ በ191ዐ አንዲት መነኩሲት ከተረከችላት ታሪኳ የተገኘ ነው፡፡ በልጅነት ዕድሜዋ በባሪያ ንግድ ምክንያት በእጅና በእግር ብረት ታስራ ከመንደሯ ተወሰደች፣ ከብዙ ስቃይ በኋላ በጣሊያን የካኖሲያን መነኮሳት አባል በመሆን ለ5ዐ ዓመታት በምንኩስና ኖረች፡፡ ስሟ ማን እንደነበር የማታስታውሰው ይህቺ ቅድስት ፍቅር ከሞላበት ትልቅ ቤተሰብ እንደተወሰደች ትናገራለች፣ /በባሪያ ንግድ ገና በሕፃንነቷ በመወሰዷ እና በማታውቃቸው ሥፍራዎች በተለያየ ጊዜ በቤት ሠራተኛነት ማገልገሏ ለዚህ ምክንያት ሊሆን ይችላል/ የዚህች ቅድስት የትውልድ ስፍራ በምዕራብ ሱዳን የምትገኘው ዳርፉር ግዛት ውስጥ ከሚኖረው የደጁ ጐሣ ነው፡፡ በባርያ ንግዱ ወቅት ከስለትና ከጠመንጃ አፈሙዝ በመትረፏ ከአፋኞች አንዱ እንዳው በመላ "ባኪታ" ሲል ስም አወጣላት፣ ትርጉሙም "እድለኛዋ" እንደማለት ነው፡፡ ባኪታ ለአንድ ቱርካዊ የጦር አዛዥ ተሸጠች፣ በዚህ ቤት ውስጥ እጅግ ዘግናኝ የሆነ ድርጊት ተፈጸመባት፡፡ ገላዋን በስለት በመብጣት አንድ መቶ አርባ ጊዜ ነቀሷት፡፡ ቁስሉ ውስጥም ጨው ጨመሩበት፤ ከሶስት ዓመታት በኋላ የጦር አዛዡ ወደ ቱርክ በመመለሱ ባኪታ አለቃ ካሊስቶ ሌኛኒ ለተባሉ አንድ ኢጣሊያናዊ ሰው ተሸጠች፡፡ ከዚህ ቤተሰብ ውስጥ በነፃነት መኖር ቻለች፣ አሳዳሪዎቿ ደግ ሰዎች ነበሩና ስቃይ ከርሷ ራቀ፡፡ በ1889 ዓ.ም በኢጣሊያ እያለች ባኪታ ከክርስትና ሃይማኖት ጋር ተዋወቀች "ኢሉማናቶ ቼኪኒ" የተበለ ፖለቲከኛና ጸሐፊ የጌታን ሥቅለት ያዘለ መስቀል ከሰጣት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ ኢየሱስ ነገራት፡፡

ባኪታ በጥር 9 ቀን 189ዐ ዓ.ም ጥምቀት ፣ ቁርባንና ምስጢረ ሜሮን በአንድ ላይ ተቀበለች፡፡ ከሶስት ዓመታት በኋላ ስዓሊ /ፖስትላንት/ ሆና የካኖሲያን እህቶች ገዳም ተመክሮ ቤት ገባች፡፡ በዚህ መልክ "ባሪያ" የነበረችው አፍሪካዊት የሱዳን ተወላጅ በኢጣሊያ ነፃ ሆና የምንኩስና ሕይወት መኖር ጀመረች፡፡ ጥቁርነቷ በሁሉ ዘንድ ዝቅ ተደርጋ እንድትታይ ምክንያት እንደሆነ ባወቀች ጊዜ "አዎ እኔ ጥቁር ነኝ ምስኪን ጥቁር ሴት" በማለት በተደጋጋሚ ትናገር ነበር፡፡ በኢጣሊያ ሃገር ጥቁር ሆኖ መገኘት ብዙም ባልተለመደበት ወቅት ባኪታ ባላት ቅንነትና ተንከባካቢነት የአገሬው ሰው "ትንሿ ጥቁር እናታችን" እያለ ይጠራት ነበር፣ ከዚህም በላይ በአካባቢው ማኀበረሰብ እንደ ቅዱስት ትታይ ነበር፡፡ ሕይወቷ አስገራሚ ክርስቶስን የማወቅ ጉዞ በመሆኑ ለብዙዎች አስተማሪ ነበር፤ ብዙ እህት መነኮሳንን ያጽናና ነበር፡፡ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እርሷ በገዳሙ ውስጥ በመኖሯ ብቻ ገዳሙ ከቦንብ ድብደባ የድናል ብለው መነኮሳን ያምኑ ነበር፡፡ ቅድስት ባኪታ የካቲቲ 8 ቀን 1974 ዓ.ም በሳንባ ምች በሽታ ሕይወቷ አለፈ፡፡ በግንቦት 17 ቀን 1992 በብፁዕ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ብፅዕናዋ ታወጀ፣ ቅድስቲቱ ስትጠቀምባቸው የነበሩት እቃዎች በሙሉ በ1993 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ ብፁዕ ዮሐንስ ዳግማዊ እጅ በሱዳን ካርቱም በተደረገ ቅዳሴ ላይ ለሊቀ ጳጳሱ ተሰጠ፡፡ ቅድስናዋ በ2ዐዐዐ ኢዮቤልዩ ታወጀ፡፡ ቅድስት ባኪታ የተጨቆኑ ሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም ስለ ክርስቶስ መከራን በመቀበል ላይ ለሚገኙ ሁሉ ጠባቂ ቅድስት ተደርጋ ትከበራለች፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት