እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የተጠራነው ለቅድስና ሕይወት ነው

የተጠራነው ለቅድስና ሕይወት ነው

የእግዚአብሔር ዓላማ በሰው ልጆች ሕይወት ላይ እስኪፈጸም ድረስ በነገሮችና በሁኔታዎች በመረጣቸው ሰዎችና ቅዱሳን፣ በተፈጥሮና በአካባቢ በትልቁም በትንሹም በቅድስና ሕይወትን እንድናውቅና እንድንኖር ዘወትር በመለኮታዊ ኃይሉ እንድንመለከት ይፈልጋል፡፡ እውነቱን አውቀን ከእውነታው ተስማምተን በተከለልን ቅዱስ ቃል ተመርተን የእርሱ ብቻ ሊያደርገን ካሰበልን የሕይወት መንገድ ተዘናግተን እንዳንጠፋ ሊረዳን ሌት ተቀን ይተጋል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምናየው ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያምን ከሴቶች መካከል ሲመርጣት በእግዚብሔር  የተለየች፣ ለዓላማው ጽኑ ልብ ያላት፣ በሁኔታዎች የማትለዋወጥ፣ ችግሮችንና ፈተናዎችን ያለ ምንም ማወላወል የምትጋፈጥ ቅን አገልጋይቷን በተግባር ማስመስከር የቻለች ብፅእት ሆና ስላገኛት የሁላችን እናት እንድትሆን ፈቀደ፡፡ “ከጌታ የተነገረላት ያመነች ብፅእት ናት” ሉቃስ 1፡45 በድንግልናዋ የአምላክ ማደሪያ እንድትሆን እግዚአብሔር ሲመርጣት ለራሷ ሀሳብና ፍቃድ ፍኞትና ሰብአዊ ፍላጐቶቿ ልትጠቀምበት አልሞከረችም፡፡ እንዲያውም በሙሉ ፍቃዱ እርሱ እንዲገለገልባት “እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ” ሉቃስ 1፡38 አለች፡፡ ለእግዚአብሔር ባላት የተለየ ጽናት በልጇ የመስቀል ጉዞ ወቅት ለእናትነት ልቧ ሳትሸነፍ በትእግስት የእግዚብሔርን ሀሳብ በመፈጸም የስቃዩ ተካፋይ ሆናለች፡፡

በዘመናችን እንደማርያም ሁሉ በምድር ሕይወት የእግዚያብሔርን ፈቃድ በመፈጸም ለቤተክርስቲያን ታላቅ ተስፋ ለአገልጋዮች ምእመናን ወጣትና ህፃናት በጎ ምሳሌ የሆኑ በርካታ ቅዱሳንን ማግኘት ችለናል። ከነዚህም መካከል ሚያዝያ 23 ቀን 2003 ዓ.ም ብጹዕ የተባሉት ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ እግዚአብሔር በወደደው ምርጫ ሕይወታቸውን ለእርሱ በመስጠት ለዓለም ሕዝብ የቅድስና ሥራ ማሳያ ሆነዋል ዘር ጎሳና ጾታ፣ ሀይማኖት ሳይለዩ ለሰው ልጆች መብት መከበር የቆሙና አያሌ መልካም ስራዎችን የሰሩ አባት ናቸው። ብጹእነታቸው የተቀበሉትን ጸጋ በመጠቀምና የክርስቶስን ምድራዊ ህይወት ምሳሌ በማድረግ አለምን ባስገረመ መልኩ የይቅርታን ምንነት ለሁላችን ያሳዩ ስለሰላም ቆመው እውነትን የሰበኩ መንፈሳዊ ህይወትን ተላብሰው እና ኖረው የብዙዎችን ነፍስ ወደ አምላክ የመለሱ ታላቅ የእግዚአብሄር አገልጋይ ናቸው። "ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።" ማቴ 5.5

ቅድስት ቤተክርስቲያን ለዘመናት ልጆችዋን  በማስተማር ለተቀደሰ ህይወት እንዲበቁ ታደርጋለች እኛም የቅድስና ሕይወት ለመኖር እንድንበቃ በማይታበይ ፍቅሩ ወደዘላለማዊ ህይወት እንድንጓዝ በነጻነት ለፈቀደልን አምላክ ሕይወታችንን አሳልፈን መስጠት ይኖርብናል፡፡ እንደተጠራንበት መጠን እግዚአብሄር በጸጋ ዝግጁዎች ያደርገናል፡፡ እኛም በፈቃዳችን ምላሽ በመስጠት ለቅድስና ህይወት እንድንበቃ በመንፈስ ጠንካራነት የድል አክሊል ተሸላሚዎች እንድንሆን እውነተኛ ወደሆነው ክርስቲያናዊ ህይወት በመመለስ የመንግስቱ ተጋሪዎች ልንሆን ይገባናል፡፡

ምንጭ፡- ፍቅርና ሰላም ግንቦት ፳፻፫ ዓ.ም.

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት