እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ቅዱስ ዮሴፍ ሞስካቲ

ቅዱስ ዮሴፍ ሞስካቲ

Giuseppe Moscattiዮሴፍ ሞስካቲ ህክምናን እንደ ጥሪ በመመልከት ልክ የምስጢረ ክህነትን አገልግሎት እንደሚፈጽም የሚሠራ የተለየ ዶክተር ነው፡፡ በናፖሊ ምስራቃዊ ክፍል በምትገኝ ቤኔቬንቶ በምትባል ቦታ ወግ አጥባቂ ከሆነ ቤተሰብ ተወለደ፡፡ አባቱ ልዩ የህግ ሰው እና ዳኛ ሲሆን ዮሴፍ 17 ዓመት ሞልቶት እስከሞተበት ዕለት ቤተሰባቸው በኢኮኖሚ ረገድ ያድግ ነበር፡፡ በተመሳሳይ ዓመት ወደ ህክምና ትምህርት ቤት የገባው ዮሴፍ ከስድስት ዓመታት የጥናት ጊዜ በኋላ በህክምና ዘርፍ ተመርቶ በአካባቢው በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ መስራት ጀመረ፣ በኋላም የፖፖሎ ቅድስት ማርያም ወደሚባል በፈውስ አልባ ህመም የተጠቁ ሰዎች ባሉት ሆስፒታል ውስጥ መስራት ጀመረ፡፡

ጊዜው መንፈሳዊው እና ቁሳዊው የ19ኛ ክፍለ ዘመን ሳይንሳዊ ዓለም በየተለያየ ጐራ ሰው ማለት ምን ማለት ነው? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ በመስጠት የተፋጠጡበት ጊዜ ነበር፡፡ እንዲህ ያለው መላ ምት ከመሰራጨቱ በፊት ዮሴፍ ባለው ጥልቅ እምነት መንፈሳዊውን ዓላማ በመከተል ዘወትር በሽታውን ብቻ ሳይሆን የሰውን ልጅ ለማከም ይፈልግ ነበር፡፡ ለተማሪዎቹም እንዲህ ሲል ፅፏል "አካልን ብቻ ሳይሆን ነፍስን ጨምር መንከባከብ እንዳለባችሁ በጥብቅ አስታውሰ፣ ለመድሃኒት ቀማሚው በሚላከው ተራ የመድሃኒት ማዘዣ ብቻ ሳይሆን በመምከርና መንፈሳቸውን እውነት በማስገንዘብ ጭምር ነው፡፡" በእያንዳንዱ ስቃይ ውስጥ ባለ ህመምተኛ ግለሰብ ውስጥ ክርስቶስን የማመላከት እንጅ ሩህሩህ ሃኪም ነበር፡፡ በ19ዐ6 በሞሱቪየስ ተራራ ላይ እሳተ ጐመራው ሲፈነዳ ከተራራው ግርጌ በሚገኘው ሆስፒታል ውስጥ በሽተኞችን ለማዳን በሚደረገው ጥረት ውስጥ የራሱን ህይወት እንኳን አደጋ ላይ ሲወድቅ ያለውን ጥልቅ እንክብካቤ አሳይቷል፡፡ ከሆስፒታሉ ብዙኃን ትተውት ሲኮበልሉም ከጥቂቶቹ ጋር ሆስፒታል ወደ አመድ ከመለወጡ የመጨረሻቹ ደቂቃ ድረስ ታግሏል፡፡ ዮሴፍ ሞስካቲ አንድ ማለዳ እንደተለመደው መሥዋዕተ ቅዳሴውን ተካፍሎ፣ ቅዱስ ቁርባኑን ተቀብሎ በሽተኞቹን በመጐብኘት ላይ ሣለ ወደ ጌታው ደስታ ገባ፡፡

በሥርዓተ ቀብሩ ላይ የናፖሊ /ኢጣሊያ/ ከተማ ሰዎች እንዲህ አሉ "ዓለም አንድ ቅዱስ ሰው ስላጣች እናለቅሳለን፣ ናፖሊ የመልካም ነገሮች ሁሉ ምሳሌ የሆነውን አጥታለችና ምስኪን ሕመምተኛ ድሆች ሁሉንም ነገር አጥተዋል፡፡" የቅዱስ ዮሴፍ ምስካቲ ብፅዕና የታወጀው እ.ኤ.አ ሕዳር 16 ቀን በር.ሊ.ጳ. ጳውሎስ 6ኛ ሲሆን ቅድስናው የታወጀው በብፁዕ ር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ጥቅምት 25 ቀን 1987 ዓ.ም ነው፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት