እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የአንጾኪያው ቅዱስ ኢግናጢዮስ

የአንጾኪያው ቅዱስ ኢግናጢዮስ

ቅዱስ ኢግናጢዮስኢግናጢዮስ ትውልዱ በሲርያ ሲሆን የሮማ ዜግነት እንደነበረው ይታመናል፡፡ በ69 ዓ.ም ገዳም ጳጳስ ሆኖ እስከተቀባበት ጊዜ ድስ ስለሕይወቱ ይህ ነው ተብሎ በግልፅ የሚታወቅ ነገር አልነበረውም፡፡ በዘመነ ጵጵስናውም ቢሆን የእርሱ ክርስትና ያስቆጣቸው ሰዎች በሮም ወታደሮች ጥበቃ ወደ ሮም እንደላኩት ከሚያስረዳው ታሪኩ ውጪ ሌላ ነገር አልነበረም አንዳንዶች ይህ ሰው የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙር የነበረ በመሆኑ በሐዋርያት እና እነርሱን ተከትሎ ከመጣው ተውልድ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበረው ይጠቅሳሉ እርሱም ስለራሱ ሲናገር ‹‹ እኔ የእግዚአብሔር ኩሊ ወይም ተሸካሚ ነኝ›› ይል ነበር ስለርሱ በይበልጥ የታወቀው ሊገደል ወደ ሮም በመሄድ ላይ ሳለ "ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት" በጻፈው መልዕክቱ አማካይነት ነው፡፡ እነዚህ መልዕክቶች ለሮማው ጳጳስ ለፓሊካርፕ ካደረሱ በኋላ በእስያ ለሚገኙ አምስት አብያተ ክርስቲያናት፣ ኤፌሶን፣ ማኘስያ፣ ትራለስ፣ ፊላዴልፊያ እንዲሁም በሰሚናር ሁሉ ተሰራጭተዋል፡፡ ኢግነጢዮስ በነዚህ መልዕክቶች ውስጥ ክርስቲያኖች ለቤተክርስቲያን በመታዘዝ አንድነታቸውን እንዲጠብቁ በአጽኖት ገልፆላቸዋል እንዲሁም ቅዱስ ቁርባን የሰላም ምስጢር ሥለመሆኑ እና ከአሳሳች መምህራን ጋር ከመከራከር ራሳቸውን እንዲያርቁ መክሮአቸዋል፡፡ "በድብቅ እንደሚናከሱ እብድ ውሾች ናቸውና ሃሰተኞች መምህራን ራቁ" (ለኤፌሶን ቤተክርስቲያን የላከው መልዕክት)

ኢየሱስ ክርስቶስ የነቢያት ሁሉ ፍፃሜ በመሆኑ ከእንግደህ ወዲህ በርሱ ትዕዛዛ እንጂ በአይሁዳውያን ባህል እንዳይመሩ በጥብቅ ከማሳሰቡም በላይ ቃል ለኛ ሲል ሰብዓዊ ባሕሪን ሳይቀር በመጋራት ከእኛ እንደ አንዱ መሆኑን ያስረዳቸው ነበር፡፡

"ከዳዊት ዘር የሆነው እርሱ ከማርያም ተወለደ፣ በእውነት የተወለደ ነው፣ እንደ ሰው የሚበላ እና የሚጠጣ፣ በጴንጢናዊው ጲላጦስ ለሞት ተላልፎ የተሰጠ፣ በእውነት የተሰቀለ እና ስለ እኛ የሞተ እናም በእውነት ሞትን ድል አድርጐ የተነሣ ነው" /ለትራሚያን ቤተክርስቲያን የላከው መልዕክት/ ቅዱስ ኢግነጢዮስ ለሮማውያን በድፍረት ለሰማዕትነት ለምትሆን ሞት ዝግጁ መሆኑን ገለጸላቸው፣ "በአረመኔዎች እጅ ልውደቅ እነርሱ ይገድሉኛል እኔ ግን እግዚአብሔርን አገኘዋለሁ፣ እኔ የእግዚአብሔር የስንዴ ቅንጣት ነኝ፣ በአረመኔዎች መንጋጋ በታኘክሁ ጊዜ ለእግዚአብሔር ምርጥ ሕብስት ሆኜ እቀርባለሁ"

በደብዳቤዎቹ ውስጥ የጥንት ክርስቲያኖች በሰማዕትነት ላይ ያለችውን ነገረ-መለኮታዊ አመለካከት አንጸባርቋል፣ ይህም በአካላዊ መንገድ ጭምር ለመሠቃየት በክርስቶስ ሕማም ውስጥ ተሳትፎ በማድረግ ከርሱ ጋር ያለንን አንድነት ማጠናከር ብቻ ሳይሆን መከራንና ሞትን ሳይቀር በክርስቲያናዊ ደስታ የመቀበል አመለካከትን ማዳበር ነው፡፡ ከታሪኩ እንደምንረዳው የሮም ክርስቲያኖች ተሠባስበው ከተፈረደበት ሞት ሊያድኑት ወደ እርሱ ቢመጡም ወደ እግዚአብሔር ለመሄድ በተነሳበት መንገድ ላይ እንቅፋት ሆነው እንዳይቆሙ ነገራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ አንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ ሞተ፡፡ "የኢግነጢዮስ የሰማይ ቤት ልደት" በማለት በጥቅምት 17 ቀን በአንጾኪያ ይከበራለ፡፡ በቤተክርስቲያን የሥነ ሥዕል ጥበብ የአንጾኪያው ቅዱስ ኢግነጢዮስ ሙሉ የጳጳስ ልብስ ለብሶ ይቀርባል፣ ይህ ዓይነት ምስል በቅድስት ሶፍያ ጥንታዊ ቤተክርስቲያን እና በካርትሬስ በሚገኙ ቅርፃቅርፆች ላይ ይስተዋላል፡፡ አንዳንዱ ጊዜ ልቡን በግራ እጁ ደግፎ እንደያዘ ሆኖ ሲቀርብ በሌላ ጊዜ ደግሞ ለክርስቶስ ሰብዓዊነት ያለውን እምነት ለማሳየት ልቡ ከተፈጥሮ ቦታዎች ውጪ ሆና "ኢየሱስ" የሚለው ሥም ተፅፎባት ይቀርባል፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት