እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ቅድስት ማሪያ ጐሬቲ

ቅድስት ማሪያ ጐሬቲ

Maria Gorettiየማርያ ጐሬቲን የሚመስል የወጣት ሴት ታሪክ ብዙ ጊዜ የሚገኝ ዓይነት አይደለም፤ ሊደፍራት ከሞከረው ሰው ጥቃት ራሷን በመጠበቅ ሰለ ንጽህና የታገለችው ትግል፣ በትግሉ ከፍተኛነት ለሞት ስትቃረብ እስትንፋሷ ከመቆሙ በፊት ለሰውየው ይቅርታ ማድረጓ ታሪኳን የተለየ እና ኃይል ያለው ያደርገዋል፡፡

እርሷ በተወለደችበት ወቅት ለመሬት ከበርቴው የሚከፈለው የጉልት ገቢ መጠኑ የሚቀመስ ባለመሆኑ ቤተሰቧ የመኖርያ ስፍራውን ለመልቀቅ ተገደዱ፡፡ የመኖርያ አካባቢውን በቀየሩ በሁለተኛው ዓመት፣ የቤተሰቡ ሦስተኛ ልጅ ማርያ አስር ዓመት ሲሞላት ወላጅ አባቷ አረፈ፡፡ እናቷ በመስክ ስራ ላይ ረጅም ሰዓት ተጠምዳ ስለምትውል ማርያ ታናናሾቿን በመጠበቅ እና በመንከባከብ ጊዜዋን ታሳለፍ ነበር፡፡

ምንም እንኳን መሠረታዊ ትምህርት ለመቅሰም ባትታደልም በራሷ ፍላጐት ወደ ከተማ እየሄደች ለመጀመሪያ ቁርባን ለምታደርገው ዝግጅት የሚጠቅሟትን አዳንዳንድ ትምህርቶች ትወስድ ነበር፡፡ ግንቦት 19ዐ2 እ.ኤ.አ ሕይወቷ እስካለፈበት ድረስ በጊዜው ብዙም ባልተለመደበት ወቅት ዘወትር በየሳምንቱ ቅዱስ ቁርባን ትቀበል ነበር፡፡ /እንደ ዛሬው ቅዱስ ቁርባን በየዕለቱ አይገኝም ነበርና/ ቤተሰቧን ያስጠጉላት ባለጠጋ ቤተሰቦች ወንድ ልጅ አሌሳንድሮ በመጀመሪያ እንደ መልካም ወንድም ቢቀርባትም እያደር ግን ንጽህናዋን የሚያጐድፍ ወሲባዊ ትንኮሳን ያደርግባትና ለማንም የተናገረች እንደሆነ እንደሚገድላት ያስጠነቅቃት ገባ፡፡

እ.ኤ.አ ግንቦት 5 ቀን አሌሳንድሮ ከመስክ ውሎ ወደ ቤት ሲመለስ ጐረቤቱ ማርያ በቤቷ ውስጥ ለብቻዋ እንደሆነች አወቀ፡፡ ይህንን የክፋት አጋጣሚ መጠቀም የፈለገው ወጣቱ በመድሃኒት /ባሕላዊ/ ካሰከራት በኋላ ሊደፍራት ቢታገልም ማርያ ስለ ንጽሕናዋ ጉዳይ ቸል የምትል የዋዛ አልነበረችም፡፡

ሴት ልጅ ስለታገለችው ክብሩ የተነካ የመሰለው ወጣቱ አሌሳንድሮ በአካባቢው ባገኘው ነገር የማርያን ግንባር ተረተረው፡፡ ማርያ ወለሉ ላይ ተዘረጋች፣ በደም ተለወሰች ምንም እንኳን ወደ ሆስፒታል ብትወሰድም በቁስሉ ትልቅነት የተነሳ በቀጣዩ ቀን ወደ ጌታዋ ደስታ ለመካፈል ሄደች፡፡ እስትንፋሷ ከማረጉ በፊት ለመጨረሻ ጊዜ ቅድስ ቁርባን ስትቀበል "ስለ ክርስቶስ ፍቅር" ስትል እግዚአብሔርን እንዲሁ እንደሚያደርግላት ተስፋ በማድረግ ለአሌሳንድሮ ይቅርታ እንዳደረገችለት ተናገረች፡፡ ከዚህ በኋላ ምንም ሳትናገር አሸለበት፡፡ ወጣቱ አሌሳንድሮ ዕድሜው ለሞት ቅጣት ገና ነበርና 3ዐ ዓመታት ወህኒ ቤት ውስጥ አሳልፏል በወህኒ ቤት ሣለ ማርያ በህልሙ እየመጣች ታነጋግረው ነበር፡፡ በ1929 ብፅዕናዋን ለማወጅ ሲደረግ ወጣቱ ከእስር ነፃ በሆነበት ጊዜ ማርያ በህልም እንዳነጋገረችው እና ከእንግዲህ ወዲህ ለነፍሱ ብቻ እንዲያስብ እና እንዲህ ያለውን እኩይ ተግባር እንዳይደግም እንደለመነችው መሰክሯል፡፡ ማርያ በ1947 ብፅዕናዋ ከታወጀ በኋላ በ195ዐ በርካታ ተዓምራት በስሟ በመመዝገቡ ቅድስናዋ ታውጇል፡፡ መርያ ሕይወቷን ሳይቀር ሰውራ ነፍሷን ለዘለዓለም አግኝታለች፡፡

 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት