እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ምን ዓይነት እሳት? ትልቁ ወይስ ትንሹ?

ትልቁ ወይም ትንሹ እሳት

ትልቁ ወይም ትንሹ እሳት በሚል ርእስ በተለያየ ክፍል የምናቀርበው ይህ ጽሑፍ በአሁኑ ሰዓት በሎንዶን የዌስትሚኒስትር ሀገረ ስብከት በሆነው የፋጢማዋ እመቤታችን ቁምስና በማገልገል ላይ በሚገኙት በክቡር አባ ኤፍሬም ዓንዶም ከተዘጋጀ ጽሑፍ የተወሰደ ሆኖ በመላይቱ ቤተ ክርስቲያን የ2 ሺህን ዓ.ም. ኢዮቤላዊ ዓመት በማስመልከት ተደርጎ ለነበረው የሦስት ዓመታት ቅድመ ዝግጅት 1998 ዓ.ም. ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የተሰጠ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ይህንን ታሳቢ በማድረግ በወቅቱ የተዘጋጀ ጽሑፍ ቢሆንም ይዘቱና ፋይዳው በቀጣይነት ለእምነት ሕይወታችን የሚያግዝ ጠለቅ ባለ መልኩ በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ ያሉትን ኃይላት በእሳት በመመሰል ለጥፋትና ለዘላለማዊው እሳት የሚዳርጉንን እሳቶች ከሕይወት ሰጪው የመንፈስ ቅዱስ እሳት ጋር በማነጻጸር የተዘጋጀ ጠቃሚ ጽሑፍ ነውና ጊዜያችንን ሰጥተን ነፍሳችንን እንመግባት። ሙሉውን ጽሑፍ ማቅረብ ባንችልም እንኳ በቀጣይነት በየጊዜው እየቀጠለ የሚሄድ ጽሑፍ ነውና ዓምዱን ደጋግመን እንጎብኘው። ለክቡር አባ ኤፍሬምም ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን፤ አገልግሎታቸውን እግዚአብሔር ይባርክ ዘንድ ሁላችን በጸሎታችን እንደምናስባቸው ይሁን።

 

"እነሆ፣ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል!" ያዕ. 3፡5

 

ትንሹ እሳት

ከእናንተ መካከል አንዱ፣ እሾሆች ካሉበት፣ የመንፈስ ቅዱስን እሳት በእነርሱ ላይ ይጣልባቸው፡፡ ሌላውም ጠንካራና የደነደነ ልብ ካለው፣ ይህንኑ (የመንፈስ ቅዱስን) እሳት በመጠቀም፣ ለስላሳና ልዝብ እንዲሆን ያድርገው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

መግቢያ

እሳት ወይስ እሳት?

(ምን ዓይነት እሳት? ትልቁ ወይስ ትንሹ?)

ዓይነቱ ይለያይ እንጂ በሁሉም ስፍራ እሳት አለ! አንድ ጸሐፊ እንዳስቀመጠው ዓለም በእሳት ተያይዛለች! በሌጣ ዓይናችን እንመልከትህ ብንለው ሁሉም እሳት በግልጽ የሚታይ አይደለም፡፡ በግዙፍ ዓይናችን የሚታየን በምድጃችን ላይ የሚንበለበለው እሳት ወይም አልፎ አልፎ ቤቶችንና ታላላቅ ደኖችን ሲያቃጥል የሚገኘው ሰደድ እሳት ብቻ ነው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ከዚህ የበረታ እሳት አለ፤ ሲነድና ሲያነድ በሌጣ ዓይን ላይታይ ይችላል፡፡ ውጤቱ ግን በግልጽ ይታያል፡፡

እስካሁን ከተባለው ልንረዳው እንደምንችለው ከግዙፋዊው እሳት ሌላ መንፈሳዊ እሳትም እንዳለ ነው፡፡ ስለ መንፈሳዊ እሳት በምናስብበት ወቅትም ቢያንስ ሁለት በጣም የተለያዩ፣ እንዲያውም ተቃራኒ የሆኑ የእሳት ዓይነቶች እንዳሉ ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ እነርሱም መለኮታዊ እሳትና ሥጋዊ ወይም ሰይጣናዊ እሳቶች ናቸው፡፡ እነዚህን እሳቶች በግዙፍ ዓይን ልናያቸው ባንችልም (አልፎ አልፎ የታዩባቸውና የሚታዩባቸው ጊዜያት እንዳሉ ባይዘነጋም) በነርሱ ምክንያት በሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚከሰቱት ክስተቶች ምን ዓይነት እሳት በአንድ ግለሰብ ሕይወት ውስጥ በመንደድ ላይ እንዳለ ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ፡፡ በመለኮታዊው እሳት የተያያዘ ሰው በመንፈስ ቅዱስ ሕግ ሲመራ፣ በዲያብሎሳዊ እሳት ወይም በሥጋዊ እሳት የነደደው ደግሞ በሥጋ ሕግ ሲመራ ይገኛል፡፡ ስለዚህም ነው ቅ.ጳውሎስ "እንግዲህ በመንፈስ ኑሩ፤ የሥጋንም ምኞት አትፈጽሙ እላለሁ፡፡ ምክንያቱም የሥጋ ምኞት ከመንፈስ ምኞት ጋር ተቃራኒ ነው፤ መንፈስና ሥጋ እርስ በእርሳቸው ይቃረናሉ፤ ስለዚህ እናንተ የምትፈልጉትን ማድረግ አትችሉም፤ በመንፈስ ብትመሩ ግን የሕግ ተገዢዎች አትሆኑም" በማለት የጻፈው (ገላ 5፡ 16-18)፡፡ ይህን ካለ በኋላም የሥጋ ሥራዎችን (የሥጋ እሳትን) በአንድ ወገን የመንፈስ ቅዱስ እሳት ውጤት የሆነውን የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን ደግሞ በሌላ ወገን ይዘረዝራል፡፡ ስለነዚህ ሁለት ሕጎች በሮም 8፡1-17 ሰፋ ያለ ገለጻን ይሰጣል፡፡

በነዚህ ሁለት ዓይነት እሳቶች የተነሣ "በምድር ላይ የሰው ሕይወት ብርቱ ሰልፍ ነው" (ኢዮብ 7፡1 እይ)፡፡ ከሁለቱ እሳቶች በአንዱ መያያዝ አማራጭ የሌለው የመንፈሳዊ ሕይወት ሕግ ነው፡፡ መሃል ሰፋሪነት የሚባል ነገር እዚህ ላይ በጭራሽ አይሠራም፡፡ ምክንያቱም ለሁለት ጌቶች መገዛት ስለማይቻል ነው፡፡ ሁለት ምርጫዎች አሉ፤ ሦስተኛ ግን የለም፡፡ ወይ በመንፈስ ቅዱስ እሳት ተቀጣጥለህ መንፈሳዊ ሕይወት መኖር ወይም በሥጋዊና በሰይጣናዊ እሳቶች ተቀጣጥለህ ሥጋዊ ኑሮ መኖር፡፡ ኢዮብ የጠቀሰው ሰልፍ ብዙ ጊዜ በሰው ሕይወት ውስጥ የሚከሰተው ሰው ለሁለት ጌቶች ለመገዛት ሲሻ ነው፡፡ ትክክለኛ ምርጫን ለማድረግ የሁለቱንም እሳቶች ምንነት ማወቁ ተገቢ ስለሆነ በጥቂቱ እናያቸዋለን፡፡ አስቀድመን ስለ ትንሹ (ሥጋዊው) እሳት ጥቂት እንበል፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት