እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ትእምርተ-መስቀል /ማማተብ/

ትእምርተ-መስቀል /ማማተብ/

የክርስቶስ መስቀል የምናከብርበት ቀላሉና ግልጹ መንገድ እትምርተ-መስቀል በመሥራት /በማማተብ/ ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች የመስቀል ምልክት የሚያደርጉት ግንባራቸው ላይ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ በትልቅ ምልክት ተተካ፡፡ ይኸውም ግንባር ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው ከግንባር ወደ ደረት ከዚያም ወደ ግራ ትከሻ ከግራ ትከሻ ወደ ቀኝ ትከሻ ማድረግ ተጀመረ፡፡

የመስቀል ምልክት ማድረግ /ማማተብ/ ለክ ጋሻን ይዞ “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል?” ሮሜ 8፡35 እንደማለት ነው፡፡ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በተሰቀለበት ወቅት መስቀሉ ኢየሱስን ተሸከመው እንጂ ኢየሱስ መስቀሉን አልተሸከመውም፡፡ ስለዚህ እኛም በመስቀሉ የድጋፍ መሠረት እናገኛለን።

ትእምርተ መስቀል ማድረግ ተጨባጭ የሆነ የእምነታችን ይዘት ነው ከላይ ከግንባራችን እንጀምራለን። ይህ የሚያሳየው ሁሉም ነገር የሚጀምረው ከላይ ከሰማይ የሁሉም ነገር የመጀመሪያ ፈጣሪ የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከእግ/ር ዘንድ እንደሆነ ነው፡፡ ከዚያም እጃችን ወደ ደረታችን እናወርደዋለን፡፡ ይህም የሚያሳየው እግ/ር ከሠማይ ወርዶ በልባችን በሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው እንደሆነ ነው፡፡ ይህ ከላይ ቀጥታ የሚወርደው መስመር ምስጢረ-ሥጋዌን ያሳያል፡፡ ይህን መስመር በመከተል ከግራ ትከሻችን ወደ ቀኝ ተከሻችን መስመር እናሰምራለን። ይህ ደግሞ የሚያሳየው ሁሉንም ነገር ያገናኘውና አንድ ያደረገው መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ነው፡፡ እግ/ር በዚህ ዓለም ላይና ወደ ጎን (Horizontal) ባለን ትስስርና ግንኙነት ውስጥ የሚሰራው በመንፈሱ አማካይነት ነውና፡፡

ትእምርተ መስቀል ከማድረግ ፈንታ እኛ እራሳችን እጆቻችንን በመዘርጋት መስቀል ልንሆን እንችላለን፡፡ የሰው ልጅ እጆቹ ሲዘረጉ በጣም ውብ ነው፡ ይኸውም ወደ እግ/ር ለመፀለይ አሊያም ጎረቤቱን ለማቀፍ ነውና። የመስቀል ምልክት በቋሚነት የሚያስታውሰን ከክርስቶስ ጋር እንደተሰቀልን እና የራሳችን ሕይወት እንደማንኖር ነው፡፡ /ገላ 2፡19/

አባ ተሻለ ንማኒ - ሲታዊ

Source (This is the day the Lord has made 365 daily meditations: By Wilfrid Stinissen)

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት