እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የፋሲካ ምስጢር

ቤተክርስቲያን በቅዱስ ቁርባን ምስጢር አማካይነት ብቻ ሳይሆን በሥርዓተ አምልኮዋ ሁሉ  የክርስቶስን ፋሲካ እጅግ እውነተኛ በሆነ መንገድ ታስተላልፋለች፡፡ እኛ ደግሞ በቤተክርስቲያን አማካይነት የክርስቶስን ቸርነት በመከተል እራሳችንን መግለጥ መቀጠል አለብን፡፡

በተቀደሰው ሳምንት (ሰሙነ ሕማማት) ውስጥ ቤተክርስቲያን የክርስቶስን መከራና ሥቃይ ታስባለች ኅብረትንም ትጐናጸፋለች፤ ስለ ሰው ልጅ ኃጠአት ኢየሱስ ከከፈለው ከፍተኛ መስዋዕትነት ጋር የመለወጥና የእርቅ ቃላትን ታስተምራለች፡፡ ጌታ አስፈሪውን ሞት ድል በመንሳት ለሰዎች ደኅንነት ያለውን ቁርጠኝነት በታላቅ ክብር አሳይቷል፡፡ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ለፈጸም ከፊታችን የሚመጣውን መከራ ሁሉ በመጋፈጥ ቤተክርስቲያን አንድነትን ትፈጥራለች፡፡

በፋሲካ በሚደረሰው የቅዱስ ቁርባን ጸሎት መግቢያ ላይ “በሞቱ ሞታችንን አሸንፏል፤ በትንሣኤውም ሕይወታችንን አድሷል” የሚል ቃል ተጽፏል፡፡ ይህም የፋሲካ መልዕክት ዋነኛ ቁልፍ ነው፡፡ በኢየሱስ ሞቶ መነሣት የእኛ መሞት የተፈጥሮአዊ ይዘቱ የተጠበቀ ቢሆንም ወደ ጨለማ ምዕራፍ ወይም ወደ ምንምነት መሸጋገሪያ መሆኑ ቀርቷል፡፡ ሞት ድል የተነሳ እውነታ ሲሆን የወደፊት ሐሳባችንንና ተስፋችንን ለማጨለም ኃይል የሌለው፣ በቁጥጥር ሥር የዋለ ክስተት ሆኗል፡፡

በአንጻሩም ሐሳባችንና የወደፊት ዕቅዶቻችን ሰፋ ያለ አድማስና የመፈጸም ዕድል ሊኖራቸው የሚችለው ለእግዚአብሔር ብቻ ከሚገባውና እኛም ከሞት የተነሳው ክርስቶስ ከቀረበልን ዘለዓለማዊ ሕይወት ጋር የተጣጣመ አንድነት ሲኖረን ብቻ ነው፡፡ ከሞት ነጻ መውጣታችን፣ ሁሉንም ነገር የሚወስን ነጻነት ሲሆን ቋሚ፣ ለታሪክና ለሰው ልጅም ተስፋ ሰጪ ለሆኑ ገንቢ ዕቅዶችም መንገድ ከፋች ነው፡፡

ይህ ለእኛም እንደዚህ መሆኑን ራሳችን እንጠይቃለን፡፡ ጥቂት እምነት ላለው አማኝ ያለው እውነተኛ አመለካከት በክርስቶስ የማዳን ጸጋ የሚገኘው ዘለዓለማዊ ሕይወትን ያካተተ ነው፡፡ ለዘለዓለማዊ ሕይወት ግልጽ መሆን ማለት የአንድን ሰው አኗኗርና የአስተሳሰብን መንገድ መለወጠ ነው፤ ይህ ለውጥ በትንሣኤ ብርሃን የፋሲካን አካሄድ የተከተለ ይሆናል፡፡

ይህ ብርሃን በእኛ ሕይወት ውስጥ በጭላንጭል ሳይሆን በሮችንና መስኮቶችን በመክፈት እኛ ውስጥ ገብቶ እንዲፈነጥቅ ከፈቀድንለት እንዴት በሆንን ነበር?

ይህ ቢሆን በምንሠራበት አካባቢና በቤተሰባችን ውስጥ የሚኖረው ግንኙነት  የጋራ ችግሮቻችን፣ በተለይ ለምንወድዳቸው ለሌሎች ሰዎች ሥቃይ ያለን አመለካከት እንዴት የተለየ በሆነ ነበር፤ በትንሣኤ ብርሃን ሁሉም ነገር ትርጉም አለው፤ ሁሉም ነገር መለኮታዊ ቃና ይኖረዋል፡፡ ሁሉም በተስፋ መዳኑን ለማመን ዝግጁ ይሆናል፡፡

ምንጭ፡ ጉዞ ከጌታ ጋር

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት