እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ፈጣሪ ፍጡሩን አገለገለ

በጸሎተ ሐሙስ እለት ደቀመዛሙርቱ ለምግብ ሲታደሙ ይህ ለእርሱ የመጨረሻው እንደሆነ ኢየሱስ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር፡፡ ከዚህ የተነሳ እርሱ የሚናገራቸው ነገሮች በሙሉ ልዩ ቦታ ነበራቸው። እያንዳንዱ ቅጽበት በትርጉም የተሞላ ነበር፡፡ ኢየሱስ ውርሱን ተወ፡፡ እርሱ አንድ የቤት ሠራተኛ /አገልጋይ/ የሚሠራውን ሠራ፡፡ ይኸውም በወዳጆቹ ፊት ተንበርክኮ እግሮቻቸውን አጠበ፡፡ ይህንን ክስተት የሚነግረን ቅዱስ ዮሐንስ ሁለት ነገሮች ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡

የመጀመሪያው ትኩረቱ ለአስቆርታዊው ይሁዳ ኢየሱስን የመክዳት ሀሳብ ሠይጣን አስቀድሞ በውስጡ እንዳሳደረበት ነው፡፡ ኢየሱስ የደቀ መዛሙርቱን እግሮች ያጠበው እነርሱ በጣም ጥሩዎችና አፍቃሪዎች ስለሆኑ ሳይሆን እርሱ እስከ መጨረሻው ከማፍቀር ውጭ ሌላ በማያውቀው  ፍቅሩ ስላፈቀራቸው ነው፡፡ በእነርሱ ፊት ራሱን እጅግ ዝቅ አደረገ፡፡ ሌላው ቀርቶ አኩይ ሐሳብ ያደረበት ይሁዳ ሳይቀር ኢየሱስን /ጌታውን/ በእግሩ ሥር አየው፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ወንጌላዊው ዮሐንስ ኢየሱስ ትኩረት ማድረግ የፈለገው እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር እንደሰጠው፣ እርሱም ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ እንደመጣ፣ ወደ እርሱም እየተመለሰ እንደሆነና በዚህ ሰዓት እርሱ ራሱ አምላክ እንደሆነ ሙሉ በሙሉ ያውቅ እንደነበር ነው፡፡ የሕጽበተ እግሩ ምሳሌ ወዳጅነትን ማሳየት ወይም የመምህራቸውን ትሕትና ማሳያ ሳይሆን እግዚአብሔር በፍጡሮቹ ፊት ተንበርክኮ ማገልገሉን ነው፡፡ እግዚአብሔር የሆነው ሰው ብቻ ሳይሆን የሰው ልጆች አገልጋይ /ባሪያ/ በመሆን የመጨረሻውን ዝቅተኛ ቦታ ያዘ፡፡

የእኛን ሌሎችን የመጫንና የራሳችን መብትና ክብር የመፈለግ ዝንባሌያችን በዚህ ምስጢር ፊት ስናየው እጅግ አስቂኝና ሞኝነት ነው፡፡ እንደ እግዚአብሔር መሆን ከፈለግን አንድ መንገድ ብቻ አለን፡- ዝቅ ብለን ማገልገል!!

አባ ተሻለ ንማኒ - ሲታዊ

ምንጭ:- This is the day the Lord has made 365 daily meditations: By Wilfrid Stinissen

 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት