እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ለሚያምኑት የዘለዓለም ሕይወት ተረጋግጧል

ለሚያምኑት የዘለዓለም ሕይወት ተረጋግጧል

Tinsaeእግዚአብሔርን በሙሉ ለመግለጽ የሚበቃ አንደበት ያለን ፍጡራን መሆን ባንችልም ስለተደረገልን መልካም ነገር ሁሉ ስሙን ስንጠራ፣ ስንወድሰው፣ ስለ ኃጢአታችን ተንበርክከን ሥርየት ስንማጸነው ከምናገኘው የመተማመን የመወደድና ፍርሃት ያለማሳደር ስሜት ከሚሰጠን የውስጥ እርካታ ባሻገር በምላሹ ታላቅነቱን በሕይወት የዘወትር እንቅስቃሴያችን በጥቂቱም ቢሆን ሳንገልጸው አናልፍም፡፡ ይህ ታላቅ ስጦታ የተገኘው ደግሞ እግዚአብሔር ልጁን በእውነተኛ ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ መዳን እስከሞት አሳልፎ ሲሰጥ በተገኘው የከበረ የጽድቅ ሥጦታ አማካኝነት ነው፡፡ በተጋድሎና በጾም የአባቱን ፈቃድ ሳይታክት ለመፈጸም የተጋውን ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ስብዕና ተቀርጸን በምድር ሕይወቱና በተጓዘባቸው መንገዶች ተጉዘንና ተማርከን የዘለዓለም ሕይወት እንዲኖረን ተጋብዘናል፡፡

በዓለ ትንሣኤ ወይንም ፋሲካ ለክርስቲያኖች ሁሉ የመታደሻ ወቅት ነው፡፡ በኃጢአት የቆሸሸው ማንነታችንን አስወግደንና አሮጌ የሆነውን ልማዳችንን ጥለን የመስቀሉን ሕማማት፣ ሥቃይና መከራ ተካፋዮች ሆነን፣ "ክርስቶስንም አገኝ ዘንድ፥ በክርስቶስም በማመን ያለው ጽድቅ ማለት በእምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ጽድቅ እንጂ ከሕግ ለእኔ ያለው ጽድቅ ሳይሆንልኝ፥ በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጕድፍ እቈጥራለሁ፤ እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።" ፊሊ 3፡ 9-11 የትንሣኤ ክርስቶስ ተቀብለንና ለብሰን በጸጋው ለምልመን ወደ አዲስ ሕይወት የሚያሻግረን የመዳን ድልድይ ያየንበት የመታደሻ ወቅት ነው ትንሣኤ፡፡ በክርስቶስ መወለድ ያኘነው ተስፋ ኃይል ሆኖ በትንሣኤው ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳው ጌታ ጋር ተስማምተን ኃጢአትን በመናቅ ዘለዓለማዊ ሞትን ድል እንነሣለን ድላችንም በትንሣኤው የምንጊዜም በድን እስረኛ ኢምንት ቁስ አካል ሆኖ ላለመቅረት ከጨለማው ወህኒ የተስፋውን ጥሩር ታጥቀንና አጥልቀን ወደ ዘላለማዊና ሰማያዊ ነጻነት የምናመልጥበት መውጫ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አዘጋጀልን፡፡

ለሕይወት የምንሰጠው ፋይዳ ትርጉም የለሽ የሚሆነው ለመጪው ዘመን ታላቅ ራዕይ ሰንቀን ስንጓዝ ነው፡፡ በዚህም ኢየሱስ ክርስቶስ "እናንተ አባቴ የባረካችሁ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ" ማቴ 25፡ 34 በማለት የመጪውን ዘመን ብሩህነት ከምድር ኑሮአችን ባሻገር ዘለዓለማዊ ሕይወት እንድንወርስ ይጋብዘናል፡፡ የሰው ዘር ሁሉ መጨረሻውም ይሁን ግቡ እግዚአብሔርን ካደረገ "የእግዚአብሔር ሃሳብ ግን ለዘለዓለም ይጸናል፤ የልቡም አሳብ ለትውልድ ሁሉ ነው" መዝ 33፡11 እያለ ቃሉን ያጸናልናል፡፡ ሞት በታላቁ ኃይል ድል ተመቷልና ሳናወላውል አቋማችንን አጠንክረን ወደ ማይሻረው፣ ጥልቅ በሆነውና ሕያው ሕይወት በሚሰጠው በትንሣኤው ጌታ ላይ መተማመኛችንን ማጽናት ይገባናል፡፡ ምክንያቱም የዛሬ ድርጊታችንና ማንነታችን የነገ ቀጣይ የሕይወት እጣ ፈንታችን መሰረት የምናስይዝበት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

የድል አድራጊነት መታሰቢያ በሆነው በዚህ የትንሣኤ በዓል ከምንጊዜም በላቀ ምሥጋናችንን፣ አምልኳችንን፣ እልልታችንን ብሎም ሙሉ ማንነታችንን የምናቀርብበት፣ እንደፈቃድህ ብለን ፈቃዳችንን የምንተውበት፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ምሬት ለሰው ልጆች ሁሉ መዳን ምክንያት በሆን የሕይወት ምሥክርነት በኑሮአችን የምንሰጥበት፣ ፍጹም መንፈሳዊ ብርታት አግኝተን የልቦናችን የበጎነት፣ የፍቅር፣ የእውነት፣ የትህትናና የሰላም መዝገብ ከፍ ብሎ የሚታይ እንዲሆንልን ጽኑ ቁርጥ ፈቃድ እናድርግ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ሁላችሁም እኔን ስሙ አስተውሉም" ማር 7፡14 ብሎ እንዳስተማረን አንዲት ቅዱስት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያንም ቅን የእግዚአብሔር አገልጋዮችን በእምነት በማጽናት እንዲሁም ምሥጢራትን አዘውትረን በመጠቀም ከክፉ ሞት እንድንርቅ ትመክረናለች ትጠብቀናለች፡፡

ምንጭ፡ ፍቅርና ሰላም መጋቢት 2004 ዓ.ም.

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት