እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ቤዛችሁ ሕይወታችሁ፣ ትንሣኤያችሁ እኔ ነኝ

የሳርዲሱ መሊጦን ስለ ፋሲካ ከጻፈው ድርሳን የተወሰደ ንባብ - "የክርስቶስ ውዳሴ"

Christ is Risen 1

ወዳጆች ሆይ የፋሲካ ምስጢር እንዴት አዲስና አሮጌ፣ ዘለዓለማዊና ኃላፊ፣ የሚበሰብስና የማይበሰብስ፣ ሟችና ዘለዓለማዊ እንደሆነ መረዳት አለባቸው፡፡

በሕጉ መሠረት አሮጌ ነው፣ ነገር ግን በቃል መሠረት አዲስ ነው፡፡ በቀዳሚነቱ ጊዜያዊ ነው፣ ነገር ግን በጸጋው ዘለዓለማዊ ነው፡፡ በበጉ መሰዋት ጠፊ ነው፣ ነገር ግን በአምላክ ሕይወት ነዋሪ ነው፡፡ በመሬት ውስጥ በመቀበሩ ምክንያት ሟች ነው፣ ነገር ግን ከሙታን በመነሣቱ ዘለዓለማዊ ነው፡፡

ሕግ አሮጌ ነው ቃል ግን አዲስ ነው፤ ቀዳሚው ጊዜያዊ ነው፣ ጸጋ ግን ዘለዓለማዊ ነው፣ በጉ ጠፊ ነው አምላክ ግን ኗሪ ነው እርሱ እንደ በግ ተሠዋ ሆኖም እንደ አምላክ ተነሣ፡፡እንደ በግ ወደ ማረጃው ስፍራ ተነዳ፣ ነገር ግን በግ አልነበረም፣ ድምፅ እንደሌለው ጠቦት ነበር፣ ነገር ግን ጠቦት አልነበረም፡፡ ምስሉ አልፎ እውነቱ ተገልጧል፡፡ በጠቦቱ ፋንታ የመጣው እግዚአብሔር ነው፣ በበጉ ፋንታ የመጣው ሰው ነው፣ ይህም ሰው ሁሉንም ነገሮች የሚይዘው ክርስቶስ ነው፡፡

ስለዚህ የበጉ መሰዋት የፋሲከ አከባበርና የተጻፈው ሕግ በክርስቶስ ከፍጻሜ ደርሰዋል፡፡ በአሮጌው ሕግ ውስጥ ያለው ሁሉም ነገርና በተለይ በአዲሱ ሕግ ውስጥ የሚገኘው ሁሉም ነገር ወደርሱ ያመለክታል፡፡

 ሕግ ቃል ሆኗል፣ አሮጌውም አዲስ ሆኗልና ትዕዛዝ ጸጋ ሆኗል፣ ምስል የነበረው እውነት ሆኗል፣ ጠቦቱ ወልድ ሆኗል በጉ ሰው ሆኗል ሰውም እግዚአብሔር ሆኗል፡፡

አምላክ ቢሆንም ሰው ሆነ፣ በስቃይ ላይ ለነበሩት ተሰቃየ፣ ለእስረኞች ታሰረ፣ ለተፈረደባቸው ተፈረደበት፣ ለተቀበሩት ተቀበረ፣ ከሙታን ተለይቶ በመነሣት "ከኔ ጋር የሚፎካከር ማነው? እስቲ ይቋቋመኝ፡፡ እኔ እስረኞችን ነፃ አድርጌያለሁ፣ ሙታንን ወደ ሕይወት ጠርቻለሁ፣ የተቀበሩትንም አስነስቻለሁ፤  እኔን የሚቃወም ማነው? ብሎ ጮኸ፡፡ "እኔ ክርስቶስ ነኝ" "ሞትን ያጠፋሁኝ፣ ጠላትን ድል ያደረግሁት፣ መቃብርን ከእግሬ በታች የረጋገጥኩት፣ ብርቱውን ያሰርኩትና ሰውን ወደ ከፍተኛው ሰማይ ቀምቼ የወሰድኩት እኔ ክርስቶስ ነኝ" ይላል፡፡

"እንግዲያውስ እናንተ በኃጢአት የረከሳችሁ ሕዝቦች ኑ፣ የኃጢአታችሁን ይቅርታ ተቀበሉ፡፡ ስርየታችሁ፣ የደኅንነታችሁ ፋሲካ፣ ለእናንተ የተሠዋሁ በግ፣ ቤዛችሁ ሕይወታችሁ፣ ትንሣኤያችሁ፣ ብርሃናችሁ፣ ደኅንነታችሁና ንጉሣችሁ እኔ ነኝ፡፡ ወደ ከፍተኛው ወደ ሰማይ እወሰዳችኋለሁ፣ ዘለዓለማዊው ወደ ሆነው አብ አቀርባችኋለሁ፣ በቀኝ እጄ አነሳችኋለሁ"

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት