እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

16 - ማርያም በኢየሱስ መስቀል አጠገብ ቆማለች

16 - ማርያም በኢየሱስ መስቀል አጠገብ ቆማለች

የእግዚአብሔር ቃል:- ዮሐንስ 19፡ 24-30

24 ስለዚህ እርስ በርሳቸው። ለማን እንዲሆን በእርሱ ዕጣ እንጣጣልበት እንጂ አንቅደደው ተባባሉ። ይህም። ልብሴን እርስ በርሳቸው ተከፋፈሉ በእጀ ጠባቤም ዕጣ ተጣጣሉበት የሚለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። 25 ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ። ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር። 26 ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት። 27 ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት። 28 ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ። ተጠማሁ አለ። 29 በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት። 30 ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።

በኢየሱስ መስቀል አጠገብ የቆመች ችናታችን ማርያም የሰማችው፤

  • ኢየሱስ ሲናገር ‹‹አንቺ ሴት እነሆ ልጅሽ፡፡ ይህችውልህ እናትህ››
  • ኢየሱስ ለወንጀለኛው የሰጠው መልስ፤ ‹‹በእውነት እልሃለሁ፤ ዛሬውኑ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ!››
  • የኢየሱስ ጩኸት ‹‹አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? አባት ሆይ እነሆ ነፍሴን በእጅህ አስረክባለሁ››
  • ‹‹ጠማኝ››
  • ‹‹ተፈጸመ››
  • የመጨረሻ የልጇ ጩኸት፤ ‹‹አየሱስ እንደገና በታላቅ ድምፅ ጮኸና ሞተ››፡፡ ከወታደሮቹ አንዱ የኢየሱስን ጎን በጦር ሲወጋውና ወዲያውኑ ከጎኑ ደምና ውሃ ሲወጣ እመቤታችን ማርያም አይታለች፡፡
  • በዚያው ምሽት እናታችን ማርያም፣ ከአርማትያሱ ዮሴፈ፣ ከኒቆዲሞስ፣ ከሚወደው ደቀ መዝሙርና ከአንዳንድ ሴቶች ጋር በመሆን፣ የኢየሱስን አስከሬን ከመስቀል አወረዱትና እንደ ወንጀለኛ እየተጣደፉ ቀበሩት፡፡
  • ቅድስ ድንግል ማርያም፣ የተመረጠች፣ በእግዚአብሔር የተወደደች፣ ፀጋን የተሞላች፣ ከሴቶች ሁሉ መካከል የተባረከች፣ የእግዚአብሔር እናት፣ እነዚህን ሁሉ ሥቃዮችና መጥፎ ገጠመኞች እያንዳንዱ ቤተሰብ የሚያሳልፋቸውን አሳልፋለች፡፡ እንደ እግዚአብሔር እናት ልዩ ጥቅም አላገኘችም እንዲሁም እርሷ እግዚአብሔር አባትን በፍጹም አላማረረችም፡፡ ክልጇ ጋር ተሳስራ ኖራለች፡፡ እርሱም እራሱ በብዙ መከራ ማለፍ ነበረበት፤ ‹‹ ›› (ዕብ 5፡ 7-8)፡፡

ተሰቃይቶ ወደ ሞት ደረጃ የደረሰውን ሰው፡- ጸሎቱን፣ የእርዳታ ጥያቄውን መስማት እና መርዳት አለመቻል ለእናታችን ማርያም የሚያሳዝን እንደነበረ አሁን ለቤተሰብ እንዴት የሚያስጨንቅ ነው!

በኢየሱስ አፍ ተስፋ መቁረጥ፣ ፍርሃትና ጭንቀት፣ ጸሎት ሆኖአል፡፡ በጣም ብዙ የተሠቃዩ ሰዎችና ቤተሰቦቻቸው የኢየሱስን ጸሎት በቃሎቻቸው ይደግማሉ፤ ‹‹አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? ለእርዳታ በብርቱ በምንጮኸበትስ ጊዜ ስለምን ከእኔ ራቅህ? አምላኬ ሆይ ቀኑን ሁሉ ወደ አንተ እጮኸለሁ አንተ ግን አትሰማኝም፣ ሌሊቱን ሁሉ እጣራለሁ፣ እረፍትም የለኝም … ›› (መዝ 22)

በሥቃይ ጊዜ እናት የሚሠቃዩትን ሰዎች ጥላ አትሄድም፡፡ እርሷ ራሷ በዛ ቦታ መገኘት የሚያስፈልግበትን ጊዜ ታውቃለች፡፡

ማርያም፣ በልጁ መስቀል ሥር ቆማ ነበር፡፡ አሁን እኛን ለብቻችን አትተወንም፣ በተለይም የእርሷን ሕልውና፣ ፍቅርንና ጸሎት በምንፈልግበት ጊዜ፣ እርሷ የእኛን አቤቱታ ትሰማለች፤ ‹‹ለኛ ለኃጢአተኞች አሁንም በሞታችን ጊዜ ለምኝልን››፡፡ እርሷ የእኛን ጸሎት ለልጇ ታቀርባለች፣ በእርሱ አማካይነት ለእግዚአብሔር አብ ጸሎታችንን ታቀርባለች፡፡ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ያደረገውን እንድናደርግ ትጋብዘናለች፤

ሀ/ ከእግዚአብሔር ጋር እንድናስታርቅ (ክርስቶስ ለወንጀለኛው ይቅርታ እንዳደረገ)፤

ለ/ የኢየሱስ የመጽናኛ ቃላት እንድንቀበል፤ ‹‹በእውነት እልሃለሁ ዛሬውኑ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ!››

ሐ/ ሞት አፋፍ ስንደርስ የኢየሱስን ጸሎት እንድንደግም፤ ‹‹አባት ሆይ እነሆ ነፍሴን በእጅህ አስረክባለሁ››፡፡

 

እንጸልይ፡-

አባት ሆይ፣ አንተ በምህረትህና በፍቅርህ እናተችን ማርያምን በልጁህ መስቀል ሥር መቆም እንድትችል አደረግህ፡፡ እናታችን ማርያም በጭንቃችን፣ በኃጢአታችንና ተስፋ በምነቆርጥበት ጊዜ አጠገባችን እንድትሆንና በዚያው እኛ ሁል ጊዜ በፍቅርህ መታመን እንድንችል፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት