እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

11- ሌላው ደቀ መዝሙር፤ ‹‹ኢየሱስ የሚወደው ደቀ መዝሙር››

11

ሌላው ደቀ መዝሙር፤ ‹‹ኢየሱስ የሚወደው ደቀ መዝሙር››

በዮሐንስ ወንጌል በብዙ ቦታ አንድ ደቀ መዝሙር ያለ ስም፣ ‹‹ኢየሱስ የሚወደው ደቀ መዝሙር›› የሚል ሐረግ እናገኛለን፤ (ንጽ. ዮሐ 1፡ 35-40፤ 13፡ 23-26፤ 18፡ 15-16፤ 19፡ 26-27፤ 20፡ 2-8፤ 21፡ 2፣7፣20-24)፡፡

-    እርሱ እውነትን እየፈለገ ያለ ደቀ መዝሙር ነው፡፡ እርሱ አጥማቂው ዮሐንስን መከተል ጀምሮ ነበር፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ ‹‹እነሆ የእግዚአብሔር በግ›› ሲል በሰማ ጊዜ ክርስቶስን ተከተለ፡፡ እርሱ ሄዶ አየና ከእርሱ ጋር ቆየ፡፡ (ንጽ. ዮሐ 1፡ 35-40)

-    እርሱ በመጨረሻ እራት በኢየሱስ ጎን የተቀመጠና ራሱን ወደ ኢየሱስ ልብ አስጠግቶ የነበረ ደቀ መዝሙር ነው፡፡ እርሱ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠው የይሁዳ ተቃራኒ ነበር፡፡ እርሱ የኢየሱስ ልብ ያውቅ ነበር፡፡ በኢየሱስና በእርሱ መሐል ትልቅ ቅርበት፣ እምነት፣ ፍቅር፣ መረዳዳትና ስምምነት ነበራቸው፡፡ (ንጽ. ዮሐ 13፡ 23-26)፡፡

-    እርሱ ኢየሱስን በሕማማቱ ጊዜ እንደ ጴጥሮስና እንደ ሌሎች ደቀ መዛሙርት ሳይክዳው በጀግንነት ይከተለው የነበረ ደቀ መዝሙር ነው (ንጽ. ዮሐ 18፡ 15-16)፡፡

-    ለእርሱ ኢየሱስ ‹‹ይህችውልህ እናትህ›› አለ (ዮሐ 19፡ 27)

-    እርሱ ማርያምን ወደ ቤቱ ወሰዳት፡፡ (ዮሐ 19፡ 27)

-    እርሱ ስለ ኢየሱስ ሞት ምስክር ነበር፡፡ (ዮሐ 19፡ 30)

-    እርሱ ፋጥኖ የሮጠና ቀድሞ ወደ መቃብሩ ደርሶ ጴጥሮስን የጠበቀ ደቀ መዝሙር ነው፡፡ ጴጥሮስ ወደ መቃብር ገብቶ ካየ በኋላ እርሱም ገብቶ አየና አመነ፡፡ (ዮሐ 20፡ 2-8)

-    እርሱ ከሞት የተሳውን ኢየሱስን ያወቀ፣ ኢየሱስ እስኪመጣ የጠበቀና ስለ ክርስቶስ የመሰከረ ደቀ መዝሙር ነው (ንጽ. ዮሐ 21፡ 2፣7፣20-24)

ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀ መዝሙር የእወነተኛ ተምሳሌትና ኢየሱስን የተቀበለና በስሙ ያመነ አርአያ የሚሆን ደቀ መዝሙር ሲሆን (ንጽ. ዮሐ 1፡ 12-13) ሁል ጊዜ ለኢየሱስ ታማኝ ሆኖ እስከ መጨረሻ የተከተለና ለእርሱ ምስክርነት የሰጠ ነው፣ ለዚህ ደቀ መዝሙር (ለእያንዳንዱ ክርስቲያን) ኢየሱስ እናቱን ሰጠ እና እውነተኛ ደቀ መዝሙር ስለሆነ እርሷን ወደ ቤቱና ወደ ልቡ ወሰደ፡፡ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እዚህ ጋ የደቀ መዝሙር (የክርስቶስ አካል)፣ የቤተ ክርስቲያን እናት ትሆናለች፡፡

ዮሐንስ በወንጌሉ ‘lambanin’ (‹‹ላምባነይን›› መቀበል) የሚለውን የግሪክ ቃል ሦስት ጊዜ ይጠቀማል፡፡

እውነተኛ ደቀ መዝሙር፤

  1. ኢየሱስን (ቃል ሥጋ የሆነውን) ይቀበላል (ዮሐ 1፡ 12)
  2. እናታችን ማርያምን ይቀበላል (ዮሐ 19፡ 27)
  3. እናም መንፈስ ቅዱስን ይቀበላል (ዮሐ 20፡ 22)፡፡

እውነተኛ ደቀ መዛሙር ኢየሱስን ይቀበላል፣ እስከ መስቀሉ ይከተለዋል፣ ስለ እርሱም ይመሰክራል፣ መንፈስ ቅዱስን ይቀበላል፣ እመቤታችን ቅድስተ ድንግል ማርያምንም እንደ እናት ይቀበላል፡፡

ኢየሱስ የሚወደውን ደቀ መዝሙር መምሰል እንድንችል እናታችን ማርያም እንድትረዳን እንለምናት፡፡

እንጸልይ፡-

አባት ሆይ ድንግል ማርያም የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያን እናት እንደሆነች እንደምናውጅ ሁሉ ከልጅህ ጋር ያለን አንድነት ደኅንነት እንዲያመጣልን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት