እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

4 - እመቤታችን ማርያም የተትረፈረፈ ሕይወት መንገድ ታሳየናለች

4 - እመቤታችን ማርያም የተትረፈረፈ ሕይወት መንገድ ታሳየናለች

የእግዚአብሔር ቃል፡- የመልአኩ ገብርኤል ብስራት፤ ሉቃስ 1፡ 26-38

‹‹ ›› (ማር 8፡ 34-35)

ከመልአኩ ገብርኤል ቃል በኋላ ቅድስ ድንግል ማርያም የሕይወቷን ዕቅድ በጥልቀት ተረዳች፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም፣ የእርሱ አገልጋይ በመሆን፣ ሕይወቷን ሙሉ ለእርሱ ሰጠች፡፡ ቅድስት ማርያም ለእግዚአብሔር ‹እሺ› አለች፣ እሺታዎንም አላጠፋችም፤

‹‹ ›› (ሉቃስ 9፡ 62)

እርሷ፣ እንደ ነቢያ፣ የእግዚአብሔር ቃል አገልጋይ ነበረች፡፡ እርሷ ለራሷ ምንም አልፈለገችም እግዚአብሔር እንዲከብር እንጂ፡፡ እመቤታችን እንዲህ የሚሉትን የጳውሎስን ቃላት መድገም ትችላለች፤

‹‹ ›› (1ቆሮ 2፡ 2)፡፡

በቤተሰብ ውስጥ ብዙ ችግሮችና ፈተናዎች አሉ፤ ለምሳሌ ያለን ሀብት በእኩልነት አለመጠቀም አንዳንድ ጊዜ ወደ እነዚህ ነገሮች ይወስደናል፤ እግዚአብሔር አባታችንን እንድንረሳ፣ ገንዘብን ያለአግባብ እንድንጠቀም፣ ሱሰኞች ያደርገናል፣ በፈተና ይጥለናል፣ የወንጌልን መንገድ እንድንረሳ ያደርገናል፡፡ ብዙ በቤተሰብ ውስጥ ያሉ ስቃዮች የሚመጡት ከነዚህ ችግሮች ነው፡፡ ይህ መንገድ የተትረፈረፈ ሕይወት እንድንወርስ አያደርገንም፡፡

ክርስቶስ የመጣው ሕይወት እንድናገኝና የተትረፈረፈ ሕይወት እንዲኖረን ነው (ንጽ. ዮሐ 10፡ 10)፡፡ ቅድስት ማርያም ራሷን  በመካድ፣ የራስዋንና የክርስቶስን መስቀል ተሸክማ እርሱን ተከትለዋለች፡፡ እንደ አብዘኞቹ እናቶቻችን፣ የእርሷ ሕይወት ቀላል አልነበረም፤ አለመረዳዳት፣ ብቸኝነትና ሞት ነበረ፡፡

‹‹ ›› (ሉቃ 2፡ 35)፡፡ ማርያም ተስፋዋን በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስላደረገች፣ እርሷ ከሴቶች ሁሉ የተባረከች ናት፣ መንፈሷ አዳኟ በሆነው በእግዚአብሔር ደስታ የተሞላችና ፍጽምት፣ ብስል፣ በሕይወት የተሞላችና ለሰው ልጅ ምሳሌ ናት፡፡

በቤተሰባችን ውስጥ አባቶች፣ እናቶች፣ ወጣቶ፣ ሽማግሎዎች ማርያም ያለችውን ለማለት ከወሰኑ፤ ‹‹እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነኝ፤ አንተ እንዳልህ ይሁንልኝ›› ከእናታችን ጋር መንገድ የሆነውን ክርስቶስን ከተከተሉ፣ የሚመኙትንና የተትረፈረፈውን ሕይወት ያገኛሉ፡፡

እንጸልይ፡-

ሁሉን የምትችል አባት ሆይ፣ እምነታችንና ተስፋችንን እውነተኛ አምላክና እውነተኛ ሰው በሆነው፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደው በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ አጠንክርልን፡፡ በትንሣኤው ኃይል ወደ ዘላለማዊ ሕይወት ለመድረስ እንድንችል  በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት