If our pages are illegible, please download fonts here: Visual Geez Unicode

 

 

የገዳመ ሲታውያን ማርያም ጽዮን አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት

    

በኢትዮጵያ ውስጥ ማኅበራችን ባሉት አራት ገዳማት ከአፀደ ሕጻናት እስከ ተግባረ እድ ደረጃ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ያስተዳድራል። ከነዚህም ትምህርት ቤቶቻችን መካከል አንዱ <<የገዳመ ሲታውያን ማርያም ጽዮን አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት>>  በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ካቶሊካዊ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሥር ሆኖ በሲታውያን ማኅበር መነኮሳን የሚተዳደር ካቶሊካዊ ትምህርት ሲሆን የሚገኘውም በምሥራቃዊ አዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ነው።   

    ማርያም ጽዮን ትምህርት ቤት የተመሠረተው በ1975 ዓ.ም. ሲሆን የተመሠረተውም በሲታውያን መንኮሳን በአንድ አነሰተኛ ቤት ውስጥ የአካባቢውን ሕጻናት ሰብስቦ ያለምንም ክፍያ በማስተማር ነው። ብዙም ሳይቆይ አሁን ካሉት አምስት ህንፃ /ብሎክ/ የመጀመሪያው ተገንብቶ ሥራውን መሥራት ጀመረ።

    የገዳመ ሲታውያን ማርያም ጽዮን ካቶሊካዊ ትምህርት ቤት ዓላማ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕጻናትን ያለምንም ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ጎሳዊና ፆታዊ ልዩነት ተቀብሎ ሰብአዊ፣ ግብረገባዊና ፈሪኀ እግዚአብሔር የተሞላ እውቀት እንዲገበዩና አገራቸውን በቅንነት የሚያገለግሉ ዜጎችን መፍጠር ነው።

    በዚህ ዓመት ማለትም በ2000 ዓ.ም. የትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና መምህራን ቁጥር እንደሚከተለው ነው፡

        የመጀመሪያ ሳይክል ማለትም ከ1ኛ እስከ 4ኛ     495 ተማሪዎች

       የሁለተኛ ሳይክል ማለትም ከ5ኛ እስከ 8ኛ        595 ተማሪዎች

       ጠቅላላ የተማሪዎች ቁጥር ድምር 1089 ሲሆን፤

       መምህራን 47

       ሕንፃ  5 ብሎክ

       የትምህርት ቤቱ ክፍለ ጊዜ የሙሉቀን መርኀ ግብር የተከተለ ነው።

 

    የገዳመ ሲታውያን ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ካቶሊካዊት አፀደ ሕፃናት፣ አንደኛና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት

  1. አፀደ ሕፃናት ተማሪዎች ብዛት - ወንድ 199 ሴት 183 ድምር 382
  2. ከ1ኛ-4ኛ ክፍል - ወንድ 297 ሴት 260 ድምር 551
  3. ከ5ኛ-8ኛ ክፍል - ወንድ 336 ሴት 259 ድምር 595
  4. 9ኛ እና 10ኛ ክፍል - ወንድ 139 ሴት 177 ድምር 316

አንዳንድ ፎቶዎች :-

       

 

 
 

አስተያየት፣ ጥያቄ ወይም ጠቃሚ የሚሉት ጽሑፍ ካለዎ ኢሜይል ለመላክ አያመንቱ  contact@ethiocist.org