፯ - “ከክፉ ሰውረን እንጂ”

    ፯ - “ከክፉ ሰውረን እንጂ”

ለአባታችን የምናቀርበውን የመጨረሻ ልመናም በኢየሱስ ጸሎት ውስጥ ተጠቃልሎ ይገኛል፡፡ ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም፡፡ ቃሉ እያንዳዳችንን በግል የሚካ አባባል ነው፤ ዳሩ ግን መላው የሰው ልጅ ቤተሰብ ይድን ዘንድ ከመላዋ ቤተ ክርስቲያን ጋር በመተባበር የምንጸልየው “እኛ” ነን፡፡ የጌታ ጸሎት በማያቋርጥ መልኩ ወደ ተለያዩት የእግዚአብሔር የድኀነት ዕቅድ አቅጣጫዎች ይመራናል፡፡ በኃጢአትና በሞት ትዕይንት ውስጥ ያለው የእኛ ትስስር “የቅዱሳን ሱታፌ” ወደሆነውና በክርስቶስ ሥጋ ወደሚገለጸው አንድነት ይለወጣል፡፡

በዚህ ልመና መሠረት ክፋት ረቂቅ ነገር አይደለም፤ ነገር ግን አንድ አካልን፣ ሰይጣንን፣ ክፉውን፣ እግዚአብሔርን የሚቃወመውን መልአክን ይመለከታል፡፡ ሰይጣን ከእግዚአብሔር እቅድና በክርስቶስ ከሚፈጸመው የድኅንነት ሥራው ፊት “ራሱን የሚጥለው /መሰናክል የሚሆነው/” ነው፡፡

“ሰይጣን ከመጀመሪያውም ነፍሰ ገዳይ … ሐሰተኛና ከሐሰት አባት” “ዓለምን ሁሉ የሚያስተው” ነው፡፡ ዮሐ 8፡44፣ ራእ 12፡9  በእርሱ ምክንያት ኃጢአትና ሞት ወደ ዓለም ገቡ፡፡ “ምርሱ በማያዳግም ሁኔታ ድል በመሆኑም ፍጥረት ሁሉ “ኃጢአትና ሞት ከሚያስከትሉት ጥፋት” ነፃ ይወጣል፡፡ አሁን “ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን እንዳያደርግ፣ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የተወለደው እራሱን እንዲጠብቅ ክፉም እንዳይነካው እናውቃለን፡፡ የእግዚአብሔር እንደሆንን ዓለምንም በሞላው በክፉ እንደተያዘ እናውቃለን፡፡” 1ዮሐ 5፡18-19

ኃጢአታችሁ ይደመሰስላችሁና ይቅርታ ያደረገላችሁ ጌታ ወደ ኃጢአት መምሪት የለመደው ባለጋራ እንደያስደነግጣችሁ ከጠላታችሁ ከዲያቢሎስ ሽፍጦች ይከላከልላችኋል፣ ይቀብቃችኋልም፡፡ ራሱን በእግዚአብሔር የሚሰጥ ሰው ዲያቢሎስን አይፈራም፡፡ በእውነትም “እግዚአብሔር የእኛ ከሆነ ከቶ የሚቃወመን ማነው?”

ኢየሱስ ሕይወቱን ስለእኛ ይሰጥ ዘንድ በገዛ ፍቃዱ ራሱን ለሞት አሳልፎ በሰጠበት ሰዓት “በዚሁ ዓለም ገዥ ላይ” የማያዳግም ድል ተገኘ፡፡ የዚህ አለም ፍርድ ይህ ነው፡፡ የዚህ ዓለም ገዥም “ወደ ውጭ ይጣላል” ዮሐ 12፡31፤ ራእ 12፡11 እርሱ “ሴቲቱን ቢያሳድዳትም” ራእ 12፡13-16 እርሷ በመንፈስ ቅዱስ “ጸጋ የተሞላች” እና በመንፈስ ቅዱስ ከኃጢአትና ከሞት ጥፋት የተጠበቀች /ያለ አዳም ኃጢአት የተጸነሰች፣ እጅግ የተቀደሰች፣ የአምላክ እናት፣ ሁልጊዜ ድንግል እና ወደ ሰማይ የተወሰደች/ አዲሲቷ ሔዋን ስለሆነች ሊይዛት አይቻለም፡፡ “ዘንዶውሙ በሴቲቱ ላይ ተቆጥቶ ከእርሷ ዘር የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ፡፡” ራእ 12፡17 ስለዚህ መንፈስ ቅዱስና ቤተ ክርስቲያን “ጌታ ኢየሱስ ሆይ፣ ና!” እያሉ ይጸልያሉ፤ የእርሱም መመጣት ከክፉው ያድነናልና፡፡

ከክፉው ለመዳን በምንለምነበት ጊዜ ባለቤታቸውና አነሳሻቸው እርሱ ከሆነ ካለፉት፤ ካሁንና ከወደፊት ክፋቶች ነፃ እንሆን ዘንድም እንፀልያለን፡፡ ቤተክርስቲያን በዚሁ በመጨረሻው ልመና የአለምን ችግር ሁሉ በአብ ፊት ታቀርባለች፡፡ እርሷ የሰውን ልጅ ከከበቡት ክፋቶች ነፃ ለማውጣት እንዲሁም እጅግ የከበረውን የሰላም ስጦታና የክርስቶስ ዳግም ምጽአት ትእግስት በሞላበት ተስፋ የምንጠባበቅበትን ጸጋ ለማግኘት ትጸልያለች፡፡ በዚህ አይነት በመጸለይ ቤተክርስቲያን “የሞትና የሲኦል መክፈቻ” ባለቤት በሆነው “ባለውና በነበረው በሚመጣውም ሁሉንም በሚገዛ ጌታ አምላክ” በእምነት በትህትና የሁሉንም ሰውና የሁሉንም ነገር በአንድነት መሰባሰብ ትጠብቃለች፡፡

ጌታ ሆይ ከክፉ ሁሉ እንድታድነን እንለምንሃለን፤ በዘመናችን ሰላምን ስጠን፡፡ በምህረትህ በመታገዝ የተቀደሰውን ተስፋና የአዳኛችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣት በመጠባበቅ፣ ሁልጊዜ ከኃጢአት ነፃ እንድንሆንና ከጭንቀትም እንድንጠበቅ አድርገን፡፡