እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

፪ - "መንግሥትህ ትምጣ"

    ፪ - መንግሥትህ ትምጣ

በአዲስ ኪዳን basileia /ባዚሌያ/ የሚለው ቃል “ንጉሥነት” /የነገር ስም/ መንግሥት /ተጨባጭ ስም/ ወይም “ግዛት” የድርጊት ስም ተብሎ ሊተረጐም ይችላል፡፡ የእግዚአብሔር መንግሥት ያለችው ከፊታችን ነው፡፡ ሥጋ በሆነው ቃል አማካይነት ወደ እኛ ቀርባለች፤ በመላው ወንጌል ውስጥም ተሰብካለች፤ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤም ወደ እኛ መጥታለች፡፡ የእግዚአብሔር መንግስት ከጸሎት ሐሙስ ጀምሮ በቅዱስ ቁርባንም አማካይነት በመካከላችን ናት፡፡ መንግሥቱ ክርስቶስ ለአባቱ በሚያስረክባት ጊዜ በክብር ትመጣለች፡፡

እንዲያውም … የእግዚአብሔር መንግሥት ማለት በእየዕለቱ እንዲመጣ የምንሻውና አመጣጡም በፍጥነት እንዲገለጥልን የምንመኘው ክርስቶስ ሊሆን ይችላል፡፡ እርሱ ትንሣኤያችን ነውና፤ በእርሱ እንነግሣለንና እርሱ የእግዚአብሔር መንግሥትም ተደርጐ ሊወሰድ ይችላል፡፡ St.Cyprian, De Dom. Orat. 13 PL 4. 528A.

ይህ “ጌታ ሆይ! ና!” /ማራናታ/ የሚለው ልመና “ና! ጌታ ኢየሱስ” እያሉ የሚጮኹት የመንፈስና የሙሽራይቱ ጥሪ ነው፡፡

ለመንግሥቱ መምጣት እንድንጸልይ የታዘዘ ባይሆንም፣ ተስፋችንን ለመጨበጥ ጉጉት ስላለን፣ ይህንን ጥሪ በሙሉ ፈቃደኛነት ባሰማን ነበር፡፡ የሰማዕታት ነፍሳት ከመሠዊያው በታች ሆነው “ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ እስከመቼ ድረስ አትፈርድም? ደማችንንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከመቼ አትበቀልም? እያሉ በታላቅ ድምፅ ይጮኻሉ /ዮሐ. ራዕይ 6፡1ዐ/፡፡ “ፍርዳቸው የሚሰጣቸውማ  በዓለም መጨረሻ ላይ ነው፡፡ ስለዚህ ጌታዬ ሆይ በተቻለ ፍጥነት መንግሥትህ ትምጣ”፡፡ Tertullian, De orat. 5 PL 1. 1159A

በጌታ ጸሎት ውስጥ “መንግሥትህ ትምጣ” የሚለው ሐሳብ የሚያመለክተው በይበልጥ በክርስቶስ መመለስ የሚመጣውን የእግዚብሔር መንግሥት ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ሐሳብ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዓለም ያላትን ተልእበኮ ከማከናወን አያናዳትም፤ ይልቁንም በትጋት እንድተቀጥልበት ይገፋፋታል፡፡ ከጴንጤቆስጤ ጀምሮ የዚያ መንግሥት መምጣት “በዓለም ላይ ሥራውን ላይ የሚፈጽመውና ለእኛም የጸጋና ምላት የሚያስገኘው” የጌታ መንፈስ ሥራ ነው፡፡

“የእግዚአብሔር መንግሥት በመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ ጽድቅ፣ ሰላምና ደስታ ነው፡፡” ሮሜ 14፡17 የምንኖርበት የዘመን መጨረሻ መንፈስ የሚፈስስበት ዘመን ነው፡፡ ከዕለተ ጴንጤቆስጤ ጀምሮ በ”ሥጋ” እና በመንፈስ መካከል ወሳኝ እየተደረገ ነው፡፡

“መንግስትህ ትምጣ” በማለት በድፍረት መናገር የምንችለው ንጹሕ ነፍስ ብቻ ናት፡፡ ስለዚህም “በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አይንገሥ” በማለት ጳውሎስ የሚያስተላልፈው ትምህርት የሰማ በሥራ፣ በሐሳብና በቃል ራሱን ያነፃ “መንግሥትህ ትምጣ” ሲል እግዚአብሔርን መለመን ይችላል፡፡

ክርስቲያኖች መንፈስ ቅዱስ በሚለግሳቸው እውቀት በመደገፍ በእግዚአብሔር መንግሥት መስፋፋትና እነርሱ በሚሳተፉበት ሕብረተሰብ ባህል ዕድገት መካከል ያለውን ልዩነት ማወቅ አለባቸው፡፡ ሆኖም ይህ ልዩነት መነጣጠል አይደለም፡፡ ወደ ዘላለም ሕይወት ይገባ ዘንድ ለሰው የቀረበው ጥሪ ፍትሕንና ሰላምን ለማገልገል ከፈጣሪ የተሰጠውን ኃይልና ብልሃት በዚህ ዓለም ላይ በተግባር የማዋል ሃላፊነቱን የሚጫን ሳይሆን ይልቁንም የሚያጠናክር ነው፡፡

ይህ ልመና የሚቀርበውና ተቀባይነት የሚያገኘው ፍሬውንም የሚያፈራው ብፅዕናዎችን በአዲስ ሕይወት በመጠበቅ በማክበር ነው፡፡ በመስዋዕተ ቅዳሴ ህልው በሆነውና በሚሠራው በኢየሱስ ጸሎት ነው፡፡

/የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ ከቁጥር 2816-2821/

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት