3. “ዓለም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው”
- Category: አንቀጽ ፭ - ሰማይና ምድር
- Published: Sunday, 13 May 2012 21:16
- Written by Super User
- Hits: 1707
- 13 May
3. “ዓለም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው”
መጽሐፍ ቅዱስና የቤተ ክርስቲያን ትውፊት “ዓለም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው” የሚለውን መሠረታዊ እውነት ከማስተማርና ከማክበር ወደ ኋላ አይልም፡፡ ቅዱስ ቦናቬንቱራ እግዚአብሔር ሁሉን ነገር የፈጠረው “ክብሩን ለመጨመር ሳይሆን ክብሩን ለማሳየትና ለማሳወቅ ነው” በማለት ያስረዳናል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ፍቅሩንና ደግነቱን ለማሳየት ካልሆነ በስተቀር ለመፍጠር ምንም ምክንያት የለውም፡፡ “ፍጥረታት ሕልውና ያገኙት የፍቅር ቁልፍ እጁን በከፈተ ጊዜ ነው፡፡” የመጀሪያው የቫቲካን ጉባኤ ይህንኑ ጉዳይ ሲያብራራ
ይህ አንድና እውነተኛ አምላክ በራሱ ደግነትና “ሁሉን በሚችል ኃይል” የራሱን ብፅዕና ከፍ ለማድረግ ወይም ፍጹምነት ለማግኘት ሳይሆን ለፍጥረታት በነፃ ፈቃዱ በሚሰጠው ጥቅም አማካይነት ይህን ፍጹምነቱን በግለጽ ለማሳየት ነው፡፡ “ከዘመናት መጀመሪያ አንስቶ ሁለቱንም ዓይነት ፍጥረታት፣ መንፈሳዊውንም ሥጋ ለሳሹንም ከምንም ነገር /እንዲሁ/ ሠራ …” ይላል፡፡
የእግዚአብሔር ክብር ዓለም የተፈጠረለትን ይህን ክስተት እውን ማድረግና ደግነቱን ማስተማርን ያካትታል፡፡ “በፍቅሩም እግዚአብሔር በጐ ፈቃዱ ሆኖ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ልጆቹ እንድንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ ይህንንም ያደረገው በተወደደው ልጁ አማካይነት በነፃ የሰጠን ክቡር ጸጋ እንድመሰገን ነው፤” ኤፌ 1፡5-6 ምክንያቱም “የእግዚአብሔርን ክብር በሕይወት ያለ የሰው ዘር ነው፤ የእግዚአብሔር መገለጥ በፍጥረት አማካይነት በምድረ ላይ ላሉ ፍጥረታት ሁሉ ሕይወትን ካስገኘ፣ ሥጋ በሆነው ቃል አማካይነት የአብ መገለጥ እግዚአብሔርን ለሚያዩ ከዚህ የቱን ያህል የላቀ ሕይወት ይሰጣቸዋል፡፡” የፍጥረት የመጨረሻው ግብ እግዚአብሔር “የሁሉም ነገር ፈጣሪ በአንድ ጊዜ የራሱን ክብርና የእኛንመ ብፅዕና በማረጋገጥ መጨረሻ ላይ ሁሉ በሁሉ መሆኑ ነው፡፡”