እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

3. “ዓለም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው”

3. “ዓለም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው”

መጽሐፍ ቅዱስና የቤተ ክርስቲያን ትውፊት “ዓለም የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ክብር ነው” የሚለውን መሠረታዊ እውነት ከማስተማርና ከማክበር ወደ ኋላ አይልም፡፡ ቅዱስ ቦናቬንቱራ እግዚአብሔር ሁሉን ነገር የፈጠረው “ክብሩን ለመጨመር ሳይሆን ክብሩን ለማሳየትና ለማሳወቅ ነው” በማለት ያስረዳናል፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ፍቅሩንና ደግነቱን ለማሳየት ካልሆነ በስተቀር ለመፍጠር ምንም ምክንያት የለውም፡፡ “ፍጥረታት ሕልውና ያገኙት የፍቅር ቁልፍ እጁን በከፈተ ጊዜ ነው፡፡” የመጀሪያው የቫቲካን ጉባኤ ይህንኑ ጉዳይ ሲያብራራ

ይህ አንድና እውነተኛ አምላክ በራሱ ደግነትና “ሁሉን በሚችል ኃይል” የራሱን ብፅዕና ከፍ ለማድረግ ወይም ፍጹምነት ለማግኘት ሳይሆን ለፍጥረታት በነፃ ፈቃዱ በሚሰጠው ጥቅም አማካይነት ይህን ፍጹምነቱን በግለጽ ለማሳየት ነው፡፡ “ከዘመናት መጀመሪያ አንስቶ ሁለቱንም ዓይነት ፍጥረታት፣ መንፈሳዊውንም ሥጋ ለሳሹንም ከምንም ነገር /እንዲሁ/ ሠራ …” ይላል፡፡

የእግዚአብሔር ክብር ዓለም የተፈጠረለትን ይህን ክስተት እውን ማድረግና ደግነቱን ማስተማርን ያካትታል፡፡  “በፍቅሩም እግዚአብሔር በጐ ፈቃዱ ሆኖ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ልጆቹ እንድንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ ይህንንም ያደረገው በተወደደው ልጁ አማካይነት በነፃ የሰጠን ክቡር ጸጋ እንድመሰገን ነው፤” ኤፌ 1፡5-6 ምክንያቱም “የእግዚአብሔርን ክብር በሕይወት ያለ የሰው ዘር ነው፤ የእግዚአብሔር መገለጥ በፍጥረት አማካይነት በምድረ ላይ ላሉ ፍጥረታት ሁሉ ሕይወትን ካስገኘ፣ ሥጋ በሆነው ቃል አማካይነት የአብ መገለጥ እግዚአብሔርን ለሚያዩ ከዚህ የቱን ያህል የላቀ ሕይወት ይሰጣቸዋል፡፡” የፍጥረት የመጨረሻው ግብ እግዚአብሔር “የሁሉም ነገር ፈጣሪ በአንድ ጊዜ የራሱን ክብርና የእኛንመ ብፅዕና በማረጋገጥ መጨረሻ ላይ ሁሉ በሁሉ መሆኑ ነው፡፡”

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት