ሰማይና ምድር

ሰማይና ምድር

የሐዋርያት ጸሎተ ሃይማኖት እግዚአብሔር "የሰማይና የምድር ፈጣሪ" ነው በማለት ሲገልጽ፣ የኒቂያ ጸሎት ሃይማኖት ደግሞ፣ ይህ የእምነት መግለጫ "የሚታዩና የማይታዩትን ሁሉ" እንደሚያጠቃልል ያብራራል፡፡

"የሰማይና ምድር" የሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ፣ የሚኖር ሁሉ፣ ፍጥረት በሙሉ ማለት ነው፡፡ በፍጥረት ውስጥ ያለውን ትስስር፣ ሰማይንና ምድርን አንድ የሚያደርጋቸውንና እንዲሁም አንዱ ከሌላው የሚለይበትን ሁኔታም ይጠቁመናል፡፡ "ምድር" የሰው ልጆች ዓለም ስትሆን፣ "ሰማይ" ወይም "ሰማያት" ጠፈርንና የራሱን የእግዚአብሔርን "መኖሪያ" "በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ" በሚለም ሐረግ የላቀ የክብር ቦታ የሆነውን "ሰማይ" ሊያመለክትም ይችላል፡፡ በመጨረሻም "ሰማይ" የሚለው ቃል ቅዱሳንና በእግዚአብሔር ዙሪያ የሚገኙ የመንፈሳዊ ፍጥረታትንና የመላእክትን "ቦታ" ያመለክታል፡፡

የአራተኛው ላተራን ጉባኤ /1215/ የእምነት መግለጫ፣ እግዚአብሔር "ከዘመን መጀመሪያ አንስቶ በአንድ ጊዜ ከምንም የስነ ፍጥረትን ሁለቱንም ሥርዓቶች፣ መንፈሳዊንና ምድራዊውን፣ ቀጥሎም ከመንፈስና ከአካል በመሠራቱ፣ የሁለቱም ሥርዓቶች ተካፋይ የሆነውን ሰው መፍጠሩን ያረጋግጣል፡፡