ዘጠነኛይቱ ትእዛዝ - የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፣ የባልንጀራህን ሚስት፣ ሌሎችንም፣ ገረዱንም፣ በሬውንም፣ አህያውንም ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ

ዘጠነኛይቱ ትእዛዝ

"የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፣ የባልንጀራህን ሚስት፣ ሌሎችንም፣ ገረዱንም፣ በሬውንም፣ አህያውንም ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ” ዘጸ. 2ዐ፡17

“ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም፣ ያን ጊዜ በልቡ ከርሷ ጋር አመንዝሯል” ማቴ. 5፡28

ቅዱስ ዮሐንስ የሥጋ ምኞት፣ የዐይን አምሮት፣ በገንዘብ መመካት በማለት ሦስት ዓይነት ምኞቶችን ወይም ፍትወቶችን ለይቶ ያስቀምጣል፡፡ እንደ ካቶሊካዊ ትምህርተ-ክርስቶሳዊ ወይም ፍትወቶችን ለይቶ ያስቀምጣል፡፡ ምኞትን፣ አስረኛው ደግሞ የሌላውን ንብረት መመኘት ይከለክላል፡፡

በቃሉ አመጣጥ መሠረት “ምኞት / ፍትወት” የትኛውንም የሰውን ጽኑ ፍላጐት ሊያመለክት ይችላል፡፡ ክርስቲያናዊ ትምህርት መለኮት የሰውን አእምሮአዊ አሰራር የሚፃረር ፍላጐት የል ልዩ ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም “ሥጋ” በ “መንፈስ” ላይ የሚያነሣው ዓመፅ ጋር ያመሳስለዋል፡፡ የሥጋ ምኞት የሚመነጨው አዳም ባለመታዘዙ ካመጣው ኃጢአት ነው፡፡ ሥጋዊ ምኞት የሰውን ሥነ ምግባራዋ ክህሎቶች ያዛባል፤ በራሱ በደል ባይሆንም፣ ሰውን ለኃጢአት ሥራ ይገፋፋል፡፡

ሰው የመንፈስና የሥጋ ጥምረት ውጤት በመሆኑ በውስጡ ብርቱ ውጥረት አለ፤ ማለትም በ “በመንፈስ” እና በ “ሥጋ” መካከል አንድ ዓይነት የዝንባሌዎች ትግል ይካሄዳል፤ ሆኖም ይህ ትግል የአዳም ኃጢአት ውርስ ነው፡፡ ይህ ትግል የኃጢአት ውጤት ከመሆኑም በላይ የኃጢአት መረጋገጫ ነው፡፡ ይህ ትግል በየእለቱ በየሚያጋጥሙ መንፈሳዊ ውጊያዎች አንዱ ነው፡፡

ለሐዋርያው ጉዳይ ለመንፈሳዊው ነፍስ ጋር የሰውን ባሕርይ እና ግላዊ አመለካከት አጣምሮ የያዘውን ሥጋ የመጥላት ወይም የመኮነን ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቁንም እርሱ የሚያተኩረው ከሥነ ምግባር አኳያ በበጐ ወይም በክፉ ሥራዎች ወይም በተሻለ አገላለጽ፣ ዘለቄታ ያላቸው ባህርያት በጐ ምግባርና ክፋት /በመጀመሪያው ሁኔታ/ የመንፈስ ቅዱስ የማዳን ሥራ መቀበል አልያም /በሁለተኛው ሁኔታ/ ያለመቀበል ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ሐዋርያው “በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ” ሲል ጽፏል፡፡