እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የልብ ንጽሕና

የልብ ንጽሕና

ልብ የሥነ ምግባራዊ ስብዕና ማደሪያ ነው፡፡ “ከልብ ክፉ ሐሳብ፣ መግደል፣ ምንዝርነት፣ ዝሙት … ይወጣልና፡፡” ማቴ. 15፡19 ከሥጋዊ ፍላጐት ጋር የሚደረግ ትግል ልብን ማንጻትንና እራስን መቆጣጠርን ይጠይቃል፤

ቅኖችና የዋሆች ሁሉ፤ የሰውን ሕይወት የሚያጠፋውን ክፋት እንደማያውቁ ጨቅላ ሕፃናት ትሆናላችሁ፡፡

ስድስተኛ ብፅዕና፤ ልበ-ንፁሖች ብፁዓን ናቸው፡፡ እግዚአብሔርን ያዩታልና፡፡ “ልበ-ንጹሖች” የሚለው ቃል የሚወክለው አዕምሮዋቸውንና ፈቃዳቸውን በተለይ በሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም በፍቅር በንጽሐ ድንግልና ወይም በወሲባዊ ታማኝነት፣ ለእውነት በሚኖር ፍቅርና በቀና እምነት ከእግዚአብሔር ቅድስና ያስተሳሰሩ ሰዎችን ነው፡፡ በልብ፣ በስጋና በእምነት ንጽሕና መካከል ዝምድና አለ፡፡

ምእመናን አንቀጸ-ሃይማኖትን ማመን ይገባቸዋል፡፡ ይህም የሚሆነው “በማናቸውም ለእግዚአብሔር ይታዘዙ ዘንድ፣ በመታዘዛቸውም በደህና ይኖሩ ዘንድ፣ በደህና በመኖራቸው ልባቸውን ያነፁ ዘንድና በንጹሕ ልብም ከሚያምኑበትን እንዲገነዘቡ ነው፡፡

“ልበ-ንጽሖች” የእግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንደሚያዩ እርሱንም እንደሚመስሉ የተስፋ ቃል ተሰጥቶአቸዋል፡፡ የልብ ንጽሕና እግዚአብሔርን ለማየት የሚያስፈልግ ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡ አሁንም እንኳን ቢሆን የልብ ንጽሕናን እግዚአብሔር በሚፈቅደው መንገድ ሌሎችን እንደ “ባልንጀሮቻችን” አድርገን ለመቀበል ያስችለናል፡፡ የልብ ንጽሕና የሰውን አካል የእኛንም ሆነ የባልንጀሮቻችንን፣ እንደ መንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ፣ እንደ መለኮታዊ ውበት መግለጫ አድርገን ለመገንዘብ ያስችለናል፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት