እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ራስን መስጠትና 3 ዓይነት ንጽሐ ድንግልና

ራስን የመስጠት አስፈላጊነት

ፍቅር የምግባራት ሁሉ ራስ ነው፡፡ በፍቅር ጥላ ስር ንጽሐ ድንግልና ሰው በስጦታነት እንደሚቀርብበት ትምህርት ቤት ይቆጠራል፡፡ የገዛ ራስን መግዛት ራስን ከመስጠት ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ ንጽሐ ድንግልና እሱን ተግባራዊ ለሚያደርገው ሰው በባልንጀራው ፊት ስለ እግዚአብሔር ታማኝነትና ርኀራኄ ምስክር ይሆን ዘንድ ያስችለዋል፡፡

ንጽሐ ድንግልና በወዳጅነት ይበልጥ ያብባል፡፡ ንጽሐ ድንግልና፣ ወዳጆቹ እንድንሆን የመረጠን ዋና በመለኮታዊ ሕይወቱ ተሳታፊዎች ያደርገን ዘንድ ፈጽሞ ራሱን አሳልፎ የሰጠ ኢየሱስን የምንከተልበትንና እሱን የምንመስልበትን መንገድ ያሳያል፡፡ ንጽሐ ድንግልና የሕያውነት ቃለ መሃላ ነው፡፡ ንጽሐ ድንግልና ከባልንጀራ ጋር በሚሆን ወዳጅነት በጐላ ሁኔታ ይገልጻል፡፡ ፆታቸው ተመሳሳይ ወይም ተቃራኒ በሆኑ ሰዎች መካከል የማዳብር ወዳጅነት ለሁሉም የላቀ ጥቅምን ያስገኛል፤ ወደመንፈሳዊ ሱታፌም ይመራል፡፡

የንጽሐ ድንግልና መልኮች

የተጠመቁ ሰዎች ሁሉ ንጽሐ ድንግልናን እንዲጠብቁ ተጠርተዋል፡፡ ክርስቲያን ሁሉ የንጽሐ ድንግልና ሁሉ አርአያ የሆነውን “ክርስቶስን ለብሷል” ገላትያ 3፡27 በክርስቶስ የሚያምኑ ሁሉ የሕይወታቸው ሁኔታ በሚፈቅደው መሠረት ንጽሕና በሰፈነበት ሕይወት እንደኖሩ ተጠርተዋል፡፡ ክርስቲያን በተጠመቀበት ዕለት ሕይወቱን በንጽሕና እንደመራ ቃል ገብቶአል፡፡

“ሰዎች ለሕይወታቸው አመቺ በሆነ መንገድ ድንግልናን ማዳበር አለባቸው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ፍጹም በሆነ መንፈስና ባልተከፋፈለ ልብ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ብቻ ለማስገዛት ሲሉ በድንግልና ወይም በተቀደሰ ብሕትውና ይኖራሉ፤ እንዲሁም የሥነ ምግባር ሕግ ለሰው ሁሉ የሚያዝዘውን የንጽሐ ድንግልናን ደንብ ተከትለው የሚኖሩ ያገቡ ወይም ያላገቡ ሌሎች ሰዎችም አሉ፡፡” ባለትዳሮች ጋብቻዊ ንጽሕናን ማክበር ይጠበቅባቸዋል፤ ሌሎች ደግሞ ከሩካቤ ተቆጥበው ንጽሕናን ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡

ንጽሐ ድንግልና ሦስት ዓይነት ነው፤

1ኛ የባልና ሚስት /የባለትዳሮች/ ንጽሕና

2ኛ ባሎቻቸው ወይም ሚስቶቻቸው የሞቱባቸው ሰዎች ንጽሕና

3ኛ የደናግል ንጽሕና ናቸው፡፡ እነኚህን እርስ በእርስ አናበላልጥም የቤተ ክርስቲያን ሥነ ሥርዓት ብልፅግና ምንጭም ይህ ነው፡፡

እጮኛሞች ከሩካቤ በመቆጠብ ንጽሐ ድንግልና እንዲጠብቁ ተጠርተዋል፡፡ እነዚህ እጮኛሞች ባለው የሙከራ ወቅት እርስ በርሳቸው ምን ያህል እንደሚከባበሩ ይገነዘባሉ፡፡ እንደሁም አንዱ ሌላውን ከእግዚአብሔር ዘንድ የመቀበል ተስፋንና የመታመንን ሥልጠና ያገኛል፡፡ እጮኛሞች የጋብቻ ፍቅር መገለጫዎችን በጋብቻቸው ወቅት ማቆየት አለባቸው፡፡ እንደዚህ በማድረጋቸውም በንጽሐ ድንግልና ለማደግ እርስ በርሳቸው ይደጋገፋሉ፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት