እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የጸሎት ውጊያ

የጸሎት ውጊያ

ጸሎት የጸጋ ስጦታ ከመሆኑም ባሻገር በእኛ በኩል የሚሰጥ ቆራጥ ምላሸ ነው፡፡ ጸሎት ሁል ጊዜ ጥረትን ይጠይቃል፡፡ ከክርስቶስ በፊት በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩት ታላላቅ የጸሎት ሰዎች እንዲሁም የአምላክ እናትና ቅዱሳን ራሱ ክርስቶስም ጸሎት ውጊያ መሆኑን ያስተምሩናል፡፡ ውጊያው ከማን ጋር ነው ውጊያው ከራሳችንና ሰውን ከጸሎት፣ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው ሱታፌ ለማራቅ የተቻለውን ሁሉ ከሚያደርገው ከፈታኙ ከሰይጣን መጥመዶች ጋር ነው፡፡ ስንኖር እንጸልያለን፣ ስንጸልይ እንኖራለንና፡፡ ዘወትር የክርስቶስ መንፈሰ በሚፈቅደው መሠረት መሥራት ካልፈለግን በስሙ የመጸለይ ልምድም ሊኖረን አይችልም፡፡ የክርስቲያኑ አዲስ ሕይወት “መንፈሳዊ ውጊያ” ከጸሎት ውጊያ ተነጥሎ አይታይም፡፡

በጸሎት ላይ ስለሚነሱ ተቃውሞዎች

በጸሎት ውጊያ ላይ በውስጣችንና በዙሪያተን የሚነሱ ጸሎትን የሚመለከቱ የተሳሳቱ ሐሳቦችን መዋጋት አለብን፡፡ አንዳንዶች ጸሎትን እንደ አንድ ስነ-ልቦናዊ እንቅስቃሴ አድርገው ያዩታል፤ ሌሎች ደግሞ ወደ አዕምሯዊ ባዶነት የሚወስድ አትኩሮትን የማጐልበት ጥረት አድርገው ይወስዱታለ፡፡ አሁንም ሌሎች ተግባራት ጋር የማይጣጣም አድርገው ስለሚመለከቱት ለእሱ የሚሆን “ጊዜ የላቸውም” እግዚአብሔርን በጸሎት የሚመጣው ከራሳቸው ብቻ ሳይሆን ከመንፈስ ቅዱስም እንደሆነ አያውቁምና፡፡

“ከዘመኑ ዓለም” አስተሳሰብ የሚመነጩ አንዳንድ አመለካከቶች ንቁ ካለሆንን በቀር ሕይወታችን ውስጥ ዘልቀው ሊገቡ የመቻላቸውን እውነት መረዳት አለብን፡፡ ለምሳሌ፣ አንዳንዶች እውነት በአእምሮና በሣይንስ የተረጋገጠ መሆን አለበት ይላሉ፤ ነገር ግን ጸሎት ንቃት ካለውና ከሌለው ሕይወታችን አልፎ አልፎ የሚፈስ ምሰጢር ነው፡፡ ሌሎች ግለሰቦች ለምርትና ለትርፍ ከፍ ያለ ዋጋ ይሰጣል፤ በእነርሱ ዘንድ ጸሎት ምንም አያስገኝምና ጥቅም የለውም አሁንም ሌሎች ደስታንና ምቾትንና የእውነት፣ የበጐውና ውብ የሆነው ሁሉ መሥፈርት በማድረግ ከፍ ከፍ ያደርጓቸዋል፤ “የውበት ፍቅር” የሆነው ጸሎት ግን ሕያውና በእውነተኛው አምላክ ክብር የሚደረስበት ነው፡፡ በመጨረሻም አንዳንዶች ደግሞ ጸሎትን የሚመለከቱት ወከባን በመጥላት ከዓለም እንደሚደረግ ሽሽት ነው፤ ነገር ግን ክርስቲያናዊ ጸሎት ከእውነት መሸሽም ይሁን ከሕይወት መራቅ አይደለም፡፡

በመጨረሻም ውጊያችን በጸሎት እንደ ውድቀት የሚያጋጥመንን መፋለም አለበት፡፡ ፍሬ-አልባነት ባጋጠመ ወቅት ተስፋ መቁረጥ፤ “ብዙ ንብረት” እያለን ሁሉንም ለጌታ መስጠት ሲገባን ያንን ባለመፈጸማችን የሚሰማን ተስፋ መቁረጥ፤ እንደፈቃዳችን ስላልተሰማን የሚፈጠርብን ቅሬታ፣ በኃጢአተኝነታችን በደረሰብን ውርደት ይበልጥ የበረታው ትዕቢት፣ ጸሎት ነፃና የማይገባን ስጦታ የመሆኑን ሐሳብ አለመቀበልና ሌሎችም ከዚህ የሚደመሩ ናቸው፡፡ መደምደሚያው ዘወትር ያው ነው መጸለይ ምን ይሠራል? እነኚህን መሰናክሎች ለመወጣት ትህትና፣ እምነትና ጽናትን እናገኝ ዘንድ መጋደል አለብን፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት