እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ጸሎታችን ውጤታማ የሚሆነው እንዴት ነው?

ጸሎታችን ውጤታማ የሚሆነው እንዴት ነው?

በድኅነት አቅድ ውስጥ የጸሎት መገለጥ የእምነት መሠረቱ በታሪክ ውስጥ በሚከሰተው በእግዚአብሔር ስራ ላይ እንደሆነ ያስተምረናል፡፡ የልጅነት አመኔታችን እጅግ የላቀ ሥራ በሆነው በልጁ ሕማማትና ትንሣኤ ተቀጣጥሏል፡፡ የክርስቲያን ጸሎት እግዚአብሔር ስለ ሰዎች ካለው መለኮታዊ ጥበቃና ከፍቅሩ እቅድ ጋር የሚደረግ ትብብር ነው፡፡

ለቅዱስ ጳውሎስ ይህ የአመኔታ ድፍረትን ያገኘው በውስጣችን ባለው መንፈስ ቅዱስ ጸሎት እና አንድያ ልጁን በሰጠው በአብ ታማኝ ፍቅር ነው፡፡ ሮሜ 1ዐ፡ 12-13፤8፡ 26-39 የሚጸልየው ልብ መለወጥ ለልመናችን የሚሰጥ ተቀዳሚ ምላሽ ነው፡፡

የኢየሱስ ጸሎት የክርስቲያንን ጸሎት ውጤታማ ልመና ያደርገዋል፡፡አርአያውም እርሱ ነው፤ እርሱ በእኛ ውስጥ ከእኛም ጋር ሆኖ ይጸልያል፡፡ የወልድ ልብ አብን የሚያስደስተውን ነገር ብቻ የሚፈልግ ከሆነ የልጅነትን ጸጋ ያገኙት ጸሎት እንደምን በስጦታዎቹ ላይ ማተኮር ይችላል?

ኢየሱስ በእኛ ቦታ ሆኖ በእኛ ስም ስለእኛ ይጸልያል፡፡ ልመናዎቻችንን ሁሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተጠቃልለው የቀረቡት ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ በጮኸ ጊዜ እና አብ በሰማው በትንሣኤው አማካይነት ነው፡፡ ኢየሱስ ስለእኛ አብን ለመማለድ የማየቋርጠው ስለዚህ ነው፡፡ ጸሎታችን በልጅነት አመኔታና ድፍረት በሰፈነበት መንፈስ ከኢየሱስ ጸሎት ጋር የተዋሐደ ከሆነ በስሙ የምንለምነው ሁሉ፣ ከማንኛውም ነገር የሚበልጠውን ስጦታዎችን ሁሉ የያዘውን መንፈስ ቅዱስን እንኳን እናገኛለን፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት