Map St Joseph Cistercians

Top Panel

እግዚአብሔር ዘወትር ያስደምመናል!

ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው የጌታችንን ልደት በዓል ምክንያት በማድረግ በቢቢሲ ሬድዮ ለመጀመሪያ ጊዜ መልእክት ማስተላለፋቸው ተገለጠ። በመልእክታቸውም ለሕሙማን፣ ለአረጋውያንና በማንኛውም ዓይነት ችግር ውስጥ ለሚገኙ ሁሉ እንደሚጸልዩ አሳውቀው፤ በቅርቡ በእንግሊዝ አገር አድርገውት የነበረውን ጉብኝት በታላቅ ፍቅር እንደሚያስታውሱትና ይህን የገና መልእክታቸውን ለሚያዳምጡ ሁሉ ዳግም መልካም ምኞት ለመግለጽ በመቻላቸውም ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል።

"በስኮትላንድ፣ ኢንግላንድና ዌይልስ የምትገኙና የእንግሊዘኛ ተናጋሪ አገር ወዳጆቼ ሆይ!

በዚህ በተቀደሰ የገና ወቅት በልዩ ሁኔታ በጸሎቴ እንደማስታውሳችሁ ለማሳወቅ እወዳለሁ። ስለ ጌታችን ልደት ስናስብ እስራኤላውያን ነጻነታቸውን ዳግም የሚመልስላቸውን መሪና መሲሕ ይጠባበቁ እንደነበር እናስታውሳለን፤ በቤተልሔም የተወለደው ሕፃን በርግጥም ነጻነትን አምጥቷል፤ ሆኖም ግን ያመጣው ነጻነት በዚያን ጊዜና ቦታ ብቻ የተገደበ ሳይሆን ለመላው ዓለምና ታሪክ ሁሉ አዳኝ ይሆን ዘንድ ነው። ይህም ነጻነት አንድም በፖለቲካ አሊያም በወታደራዊ ኃይል ያይደል በክርስቶስ የመስቀል ላይ አሳፋሪ ሞት አማካይነት ሞትን ለአንዴና ለመጨረሻ በመደምሰስ የተገኘ ነው።" ብለዋል።

ር.ሊ.ጳ. ለአዳማጮቻቸው ማንኛውንም ዓይነት የሕይወት ጨለማ ለማስወገ ወደ ኢየሱስ እንዲያቀኑ አሳስበው "አምላካችንን ለመልካምነቱ እናመስግነው፤ ከማንኛውንም ዓይነት ሸክም ነጻ እንደሚያደርገን በደስታ በአካባቢያችን መልካሙን ዜና እናብስር፣ እርሱ ተስፋና ሕይወትን ይሰጠናል።" በማለት አበረታትተዋል።

"እግዚአብሔር ለተስፋ ቃሉ ታማኝ ነው፤ ሆኖም ግን የሰጠንን ተስፋ የሚፈጽምባቸው ሁኔታዎች ሁሌም ያስደምመናል፤ ያስደንቀናል" በማለት ኢየሱስ ሕፃን ሆኖ ተወልዶ ሰው በመሆን ያዳነንን ሁኔታ የገለጹበት የአጭር ደቂቃውች የሬድዮ መልእክታቸውን ደምድመዋል።

 

ምንጭ - http://www.bbc.co.uk/news

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።