Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ሢመተ ክህነት በሲታውያን ቅ. ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን

ከህነት ዘሲታውያንበእለተ ሰንበት ጥቅት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ሁለት የሲታውያን መነኮሳት ዲያቆናት ሢመተ ክህነት አዲስ አበባ በሚገኘው ገዳመ ሲታውያን ዘቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን ተከናውኗል።

በብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ሱራፌል ደምረው እጅ ክህነት የተቀበሉት አባ ኃይለ ኢየሱስ (ታገሠ) ጳውሎስና አባ ልደተ ማርያም (ልደት) ብዛኒ ናቸው። በብዙ ካህናት ወንድሞቻቸው፣ በመነኮሳት፣ በወዳጅ ዘመዶቻቸው ታጅበው ደማቅ በሆነ መንፈሳዊ ሥርዓት የተከናወነው ሢመት ለእነርሱና ለአገልግሎታቸው ቅድስናን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለማችን ሰላመ ክርስቶስን የሚያበዛ ያድርግልን።

ለመደምደሚያም ለዚሁ ቀን መታሰቢያ በተዘጋጀው ትንሽ ሥዕል ጀርባ ላይ የሰፈረውን የአዲሶቹ ካህናት ጸሎት እንጋራ፦

“እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ!

ለዚህ ቀን ስላደረስከንና በፊትህ እንድንቆም ስላበቃኸን እናመሰግንሃለን።

የረዱንን፣ ቤተሰቦቻችንን፣ መልካም አድራጊዎቻችንን እና የገዳመ ሲታውያን አባቶቻችንንም ባርካቸው።

ከዓለማችን ይህንን አስከፊ በሽታ አርቅልን።” አሜን።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።