እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በዚህ ዓምድ ውስጥ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ጎላ ብሎ ሊታይ የሚገባው ሚና ያላቸውን ሰዎች ገድል እናካትታለን። እንደ አመቺነቱ ታሪኮቹን ለማሰባሰብ የምንሞክርበት ነውና አቀራረቡ የዘመናት ቅደም ተከተልን የተከተለ አይደለም ስለዚህም ከአንዱ ወደ ሌላው የሚሸጋገር ዓይነት ወጥ የሆነ አካሄድ ላይኖረው ይችላል።


 

የብፁዕ ገብረ ሚካኤል አጭር ሰማዕታዊ ገድል

የብፁዕ ገብረ ሚካኤል አጭር ሰማዕታዊ ገድል

ብጹዕ ገ/ሚካኤል በ 1788 በጎጃም ልዩ ስሙ ዲቦ በተባለ አውራጃ ተወለዱ። ከልጅነታቸው ጀምረው የአገራችንን ትምህርት ማለትም ዜማ፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ቅኔ ወዘተ. . . ለመማር ተሰማሩ። በትምህርት ትጋታቸውና በውጤታቸው መምህሮቻቸው በጣም አደነቁዋቸው። ይህን ሁሉ መንፈሳዊ እውቀት ካካበቱ በኋላ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር በሙሉ ልባቸው ሊሰጡ ፍላጎት ዕቅድ…

Read more: የብፁዕ ገብረ ሚካኤል አጭር ሰማዕታዊ ገድል

Write comment (0 Comments)

የቅዱስ አቡነ ያቆዕብ ዩስጢኖስ ታሪክ

የቅዱስ አቡነ ያቆዕብ ዩስጢኖስ ታሪክ


ቅዱስ አቡነ ያዕቆብ ዩስጥኖስ በ1800 እ.ኤ.አ በኢጣልያ ሳምፍል በተባለ መንደር ተወለዱ። በ1818 ዓ.ም. እ.ኤ.አ. ወደ ላዛሪስት /ማኅበረ ልኡካን/ ገዳም ገቡ። እ.ኤ.አ. በ1824 ዓ.ም. ሢመተ ክህነት ተቀበሉ። በናፖሊ ከተማ ለድሆች ወንጌልን እያስተማሩም በመንፈስና በሥጋ እያገለገሉ ሳሉ በመስከረም ወር 1838…

Read more: የቅዱስ አቡነ ያቆዕብ ዩስጢኖስ ታሪክ

Write comment (1 Comment)

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት