የገዛ ራስህን ድካም መገንዘብ
Last Updated (Friday, 26 February 2010 05:47)
ስቃይ መልስ የለውም ማለት ትርጉም የለውም ማለት አይደለም!
Last Updated (Thursday, 11 February 2010 11:01)
ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ላይ የግድያ ሙከራ ያደረገው ቱርካዊ ከማረምያ ቤት ወጣ
Independent Catholic News - Tuesday, January 19, 2010 - በ1973 ዓ.ም. በር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ላይ የግድያ ሙከራ ያደረገው ቱርካዊ ከእስር ተለቀቀ። ግለሰቡ ከዚህ በኋላ የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት ግዳጁን እንደሚፈጽምም የቱርክ መገናኛ ብዙኀን ዘግቧል።
በአሁኑ ሰዓት 52 ዓመት ዕድሜ ያለው መህሜት አሊ አጅካ በር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ላይ ባደረገው የግድያ ሙከራ በጣልያን 19 ዓመታትን በእስር ያሳለፈ ሲሆን፤ በመቀጠል ደግሞ ከዚያ በፊት የአንድ ጋዜጣ አርታዒን በመግደሉ ሌላ 10 ዓመታትን በመታሰሩ በድምሩ 30 ዓመታት በእስር ቤት ማሳለፉ ታውቋል።
ምንም እንኳ በወቅቱ በቁጥጥር ሥር ሲውል ከማንም ጋር ትብብር የሌለው ግላዊ ድርጊት መሆኑን ቢገልጽም፤ ር.ሊ.ጳጳሳትን ለመግደል ለአጅካ ምክንያት የሆነው ነገር እስካሁን ምስጢር እንደሆነ ቀርቷል። በአንድ ወቅት የቱርክ አንድ አገራዊ ቡድን አባል የነበረ ሲሆን፤ በሌላ አጋጣሚም በቡልጋርያ የደኅንነት አገልግሎት እንደሚመራ ገልጾ የነበረ ቢሆንም እንኳ በ1970ዎቹ በጣልያን 22 ወራትን የፈጀው ምርመራ መረጃ ሳያገኝለት ቀርቷል።
በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የግድያ ሙከራ የተደረገባቸው ር.ሊ.ጳ. ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ በ1975 ዓ.ም. ከአጅካ ጋር ከተገናኙ በኋላ ይቅር ማለታቸው ይታወቃል።
በተደጋጋሚ የሚታዩት ኃይለኛ ቁጡነቱና "አዲስ መሲሕ ነኝ" የሚሉት ንግግሮቹ ስለአጅካ የአእምሮ ጤነኝነት ጉዳይ ቀጣይ የሆነ ጥያቄ አስነሥተዋል። ትላንትና ከእስር ሲለቀቅ ባደረገውም ንግግር "የዓለምን ፍጻሜ አውጄያለሁ፤ በያዝነው ክፍለ ዘመን መላው ዓለም ይወድማል፤ ሁሉም ሰውም ይሞታል። እኔ ዘላለማዊው ክርስቶስ ነኝ" ሲል ተደምጧል።
Last Updated (Wednesday, 20 January 2010 21:19)
- የልደተ ክርስቶስ ድባብ በቫቲካን መንበረ ጴጥሮስ
- ተስፋችን እግዚአብሔር ነው
- ማንም ሰው ብቻውን እንዳይሆን፤ ማንም ሰው እንዳይነጠል፤ ማንም ሰው ተጥሎ እንዳይቀር
- በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ የመነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት ሕንድ ትመራለች
- በኢራቅ የአናሳ ሃይማኖቶች ህልውና
- እርቅን፣ ፍትሕ እና ሰላምን ተግባራዊ ለማድረግ ንጹሕ ልብ፣ አዲስ አመለካከትና ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት
- በሚሊየን የሚቆጠሩ ጽንስ የማስወረድ ሕጋዊነትን ተቃዋሚዎች በስፔን
- ቤተ ክርስትያን የስብከተ ወንጌል ተልእኮ ቀንን አስታውሳ ዋለች
- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ፓትሪያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ለአፍሪቃ ብፁዓን ጳጳሳት ሁለተኛው ሲኖዶስ ያሰሙት ንግግር
- ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶስክ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ያቀረቡት ሰላምታ
- የሰው ልጅ ሁሉ መመዘኛ ክርስቶስ ነው
- የአፍሪቃ ጳጳሳት ሲኖዶስ ተጀመረ








