ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ)

በቅርብ የተጨመሩ ጽሑፎች

በሚሊየን የሚቆጠሩ ጽንስ የማስወረድ ሕጋዊነትን ተቃዋሚዎች በስፔን

Pro-life

Independent Catholic News - ቅዳሜ ጥቅምት 7 ቀን 2001 ዓ.ም. መንግሥት ጽንስ ማስወረድ የሚመለከተውን የስፔን ሕግ ለማሻሻል ያቀረበውን እቅድ በመቃወም ከአንድ ሚሊየን በላይ የሚሆን ሕዝብ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጉ ተዘገበ።

እ.ኤ.አ. ከ1985 ዓ.ም. ጀምሮ እስካሁን በሥራ ላይ ባለው የስፔን ሕግ መሠረት ተገድዶ በመደፈርና አስጊ የሽል ሁኔታዎች ሲከሠቱ ብቻ ውርጃን የሚፈቅድ ሲሆን፤ አካላዊ ወይም ሥነ ልቦናዊ ጤንነትን የሚያሰጋ ሁኔታ ካለም ስፔናዊት ሴት ርግዝናዋን እንድታቋርጥ ይፈቅዳል። ይህ የሁለተኛውን አማራጭበሚመለከት በተግባር ላይ የዋለው ውርጃ ሲታይ ግን እ.ኤ.አ. በ2007 ዓ.ም. ብቻ 112,000 ጽንስ ማጨናገፍ መከናውኑ ታውቋል።

 

Last Updated (Monday, 26 October 2009 15:41)

 

ቤተ ክርስትያን የስብከተ ወንጌል ተልእኮ ቀንን አስታውሳ ዋለች

ራድዮ ቫቲካን - ቅ.አ.ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትናንት እሑድ ከሐዋርያዊ አዳራሽ መስኮት በመንበረ ቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ  ከተሰበሰቡት በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩት ምእመናን ጋር የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት ከመድገማቸው በፊት ዕለቱ የስብከተ ወንጌል ተልእኮ ቀን የሚዘከርበት እሁድ መሆኑን አስታውሰው፣ ቤተ ክርስትያን ለመላው ሰው ዘር ወንጌልን መስበክ እንደሚጠበቅባትና ቤተ ክርስትያን የምትኖረው የወንጌል የተስፋ መልእክትን ለማስተላለፈ መሆኑን አሳስበዋል። በቅርቡ በብራዚል የተገደሉት ልኡከ ወንጌል ኣባ ሩቮለቶ እና በፊሊፒንስ የታገቱት አባ ሲኖት በማስታወስም በጸሎት እና በመንፈስ እንደሚዘክሩዋቸው አረጋገጠዋል።

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ፓትሪያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ለአፍሪቃ ብፁዓን ጳጳሳት ሁለተኛው ሲኖዶስ ያሰሙት ንግግር

ቫቲካን ሬድዮ- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ጳውሎስ ለአፍሪቃ ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን ብፁዓን ጳጳሳት ሁለተኛው ሲኖዶስ በእንግድነት ተገኝተው ንግግር ማሰማታቸው ከሲኖዶስ አዳራሽ የተላለፈልን ዜና ገለጸ።
የፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ጳውሎስ ንግግር:- "በስም አብ ወወልድ ወንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፣...

Last Updated (Thursday, 08 October 2009 19:29)

 
የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 6:
Ethiopia flag 27%Ethiopia (3)
United States flag 27%United States (3)
Russian Federation flag 18%Russian Federation (2)
Canada flag 9%Canada (1)
Moldova, Republic of flag 9%Moldova, Republic of (1)
Switzerland flag 9%Switzerland (1)
11 visits from 6 countries