ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ)

በቅርብ የተጨመሩ ጽሑፎች

ለእውነት ክፍት መሆን ይገባል

ራድዮ ቫቲካን - ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ በቼክ ሪፐብሊክ አገር አቀፍ አሥራ ሦስተኛ ሐዋርያዊ ጉብኝት ፈጽመው ከትናንትና በስቲያ ወደ ካስተል ጋንደልፎ ሐዋርያዊ መንበራቸው መመለስቻው ታውቋል።
ቅዱስ አባታችን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ ከቼክ ሪፐብሊክ ርእሰ ከተማ ፕራግ አውሮፕላን ማረፍያ ሲነሡ አሸናኘት ላደረጉላቸው የቼክ ሪፐብሊክ የሃይማኖት እና የመንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣናት ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ ከአውሮፕላን ማረፍያ ሲነሡ መለኮታዊ ቁንጅና ለዓለም እንዲያንጸባርቅ ለእውነት ክፍት ትሆኑ ዘንድ እመኛለሁ ብለዋል ።
ቼክ ሪፐብሊክ የተባረከች ሃገር ናት ምክንያቱም አንጋፋዎች ሚስዮናውያን እና ሰማዕታትን ያበቀለች ቅድስት የክርስትያን እሴቶች አቀፍ ሀገር ናት ሲሉ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ ቼክ ሪፐብሊክን አወድሰዋል።
ቼክ ሪፐብሊክ በኮሚኒስት አገዛዝ ሥር በነበረችበት ወቅት የተገደለችው ቅድስት አኘሰ ዘቦኤሚያ እና በስታራ ቦስላቭ ሰማዕት የሆነውን ቅዱስ ቬንሰስላው አስታውሰዋል።

Last Updated (Thursday, 01 October 2009 22:54)

 

ር.ሊ.ጳ. በሚስዮናዊው መገደል የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ

VATICAN CITY, SEPT. 22, 2009 (Zenit.org).- ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው ባለፈው ቅዳሜ ብራዚል ውስጥ በተገደሉት ጣልያናዊ ሚስዮናዊ አባ ሩጄሮ ሩቮሌቶ ሞት ምክንያት የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ። ለማናዎስ ሊቀ ጳጳሳት ሉይስ ሶዋሬስ በላኩት የቴሌግራም ኀዘን መግለጫቸው ውስጥ ይህን "ሰላማዊ የወንጌል አገልጋይ ላይ ደስ የማይልና የጭካኔ ድርጊት" በጥብቅ በማውገዝ በጸሎት መንፈሳዊ አብሮነታቸውን ገልጸዋል።

አባ ሩቮሌቶ የተገደሉት በሰሜን ብራዚል

Last Updated (Tuesday, 22 September 2009 22:36)

 

የናዝሬቱ ኢየሱስ ላንተ ማነው?

Independent Catholic News - ኢየሱስ መንገድን ሊያሳየን ያውም ወደ ሕይወት የሚያደርሰን መንገድን እንጂ ፍልስፍና ሊያስተምረን አልመጣም፤ ይህ መንገድ የእውነተኛ እምነት መገለጫ የሆነው ፍቅር ነው" በማለት ነበር ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው ከካስተልጋንዶልፎ ባለፈው እሑድ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት አስተምህሯቸው መጀመሪያ ላይ የዕለቱን ወንጌል መልእክት ማካፈል የጀመሩት።

በመቀጠልም "የእግዚአብሔር ቃል ሁለት ወሳኝ ጥያቄዎችን ያቀርብልናል፦ የናዝሬቱ ኢየሱስ ላንተ ማነው? የሚልና እምነትህ ተግባራዊ ሆኗል ወይስ አልሆነም? የሚለው ናቸው።" ካሉ በኋላ ር.ሊ.ጳ.

Last Updated (Tuesday, 22 September 2009 22:39)

 
የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 5:
United States flag 36%United States (4)
Ethiopia flag 27%Ethiopia (3)
Russian Federation flag 18%Russian Federation (2)
Moldova, Republic of flag 9%Moldova, Republic of (1)
Switzerland flag 9%Switzerland (1)
11 visits from 5 countries