ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ)

በቅርብ የተጨመሩ ጽሑፎች

ሦስት ሺህ ሰዎችን በማዳናቸው ሚሲዮናዊው ተመሰገኑ

(Independent Catholic News) - እ.ኤ.አ. በ1994 ዓ.ም. በሩዋንዳ 800,000 ሰዎችን ሰለባ ባደረገው የጅምላ ጭፍጨፋ ወቅት ሌሎችን ከሞት ለመታደግ ላደረጉት ትልቅ አስተዋፅኦ ባለፈው ሳምንት ታላቅ አክብሮት ከተቸራቸው አሥር ሰዎች መካከል አንድ ጣልያናዊ ሚሲዮናዊ አንዱ መሆናቸው ታውቋል። 

በአሁኑም ሰዓት እዚያው ሩዋንዳ ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙት አባ ማሪዮ ፋልኮኒ የቱትሲ ጎሣ አባላትን በምሥራቅ ሩዋንዳ ሙሁራ ውስጥ በሚገኘው የቁምስና ቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በማስጠጋትና በመደበቅ በወቅቱ ከ3,000 በላይ የሆኑ ሰዎች ሕይወት መታደጋቸውን የሩዋንዳ ሬድዮ ዘግቧል።
 

ግብረ ጥንቆላን በመቃወሙ የተገደለው አስተማሪ ቅድስና

Teacher killed for opposition to witchcraft, could become South Africa's first saint | South Africa's first Saint,Cause for Beatification, Benedict Daswa, Diocese of Tzaneen,Archbishop James Patrick Green, Apostolic Nuncio in South Africa, Archbishop Angelo Amato, Prefect for Congregation for Causes of Saints(Independent Catholic News) - ከዛሬ 19 ዓመታት በፊት የጥንቆላን ነገሮች በመቃወሙ የተገደለው ደቡብ አፍሪካዊ ካቶሊክ መምህር ቤኔዲክት ዳስዋ የደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያው ቅዱስ የመሆን ሂደት ላይ መሆኑ ተዘገበ።

ብፅዕናው ይታወጅ ዘንድ የሚያግዙ 850 ገጽ ያላቸው ሰነዶች ከአምስት ዓመት በላይ ሲዘጋጁ ቆይተው የተከናወኑ ሲሆን የቅድስና ጉዳይን ወደ ሚመለከተው የቫቲካን ክፍል መንበር ኃላፊ ሊቀ ጳጳሳት አንጀሎ አማቶ ተልከዋል። ቀጣዩ ርምጃ የሚሆነው የእግዚአብሔር አገልጋይ ቤኔዲክት ዳስዋ ምስል ማዘጋጀትና በአማላጅነቱም ጸጋን ለማግኘት ጸሎት ማሳተም ይሆናል። ይህ በእንዲህ እንዳለም የደቡብ አፍሪካ ካቶሊካውያን ጳጳሳት ጉባዔ ታሪኩን፣ ሥራውንና ሕይወቱን ለማስፋፋት ያግዝ ዘንድ የእሱን አጭር የሕይወት ታሪክና ዲቪዲ እያዘጋጀ መሆኑም ታውቋል። 

ቤኔዲክት ባህላዊ እምነት ከነበራቸው ቤተሰቦች ሌምባ ከሚባል አናሳ ጎሣ የተወለደና በዚያው ያደገ ሲሆን፣ ኋላም ባብዛኛው ቬንዳ በምትባል ከተማ ኖሯል። ከነበረው ባህላዊ እምነት ወደ ካቶሊክነት የተለወጠው ለመምህርነት በመማር ላይ ሳለ ነበር። 

 

Last Updated (Wednesday, 22 July 2009 20:39)

 

አዲስ ሐዋርያዊ ወኪል በኢትዮጵያ - በነቀምት

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ የማኅበረ ልኡካን ማኅበር አባል አባ ቴኦደሩስ ፋን ሩቨን በኢትዮጵያ የነቀምት ሐዋርያዊ ወኪል እንዲሆኑ መሰየማቸውን የቅድስት መንበር መግለጫ አስታውቀ።
አባ ቴኦዶሩስ ፋን ሩቨን በኔዘርላንድ የአምስተርዳም ሀገረ ስብከት ሪስቪክ በተባለ ቦታ ግንቦት ሀያ ሁለት ቀን 1938 እ.ኤ.አ. የተወለዱ ሲሆን በ1964 ፓኒንገን በተባለ ቦታ መዓርገ ክህነት የተቀበሉ መሆናቸውን መግለጫው አመልክቷል።
አባ ቴኦዶሩስ መዓረገ ክህነት ከተቀበሉ ከአንድ ዓመት በኋላ በማኅበራቸው አማካይነት ማለትም በማኅበረ ልኡካን (ላዛሪስት) ወደ ኢትዮጵያ የተላኩ እና በሀገሪቱ ውስጥ በተለያዩ የቤተክርስትያን ሐዋርያዊ አገልግሎት የተሰማሩ መሆናቸው መግለጫው በተጨማሪ ገልጧል።  እስከ አሁን ድረስም የጂማ ቦንጋ ሐዋርያዊ አሰተዳዳሪ ሆነው መስራታቸው መግለጫው አክሎ ዘግቧል። 

 

Last Updated (Sunday, 23 August 2009 20:42)

 
የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 6:
Ethiopia flag 27%Ethiopia (3)
United States flag 27%United States (3)
Russian Federation flag 18%Russian Federation (2)
Canada flag 9%Canada (1)
Moldova, Republic of flag 9%Moldova, Republic of (1)
Switzerland flag 9%Switzerland (1)
11 visits from 6 countries