ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ)

በቅርብ የተጨመሩ ጽሑፎች

ቱርክ ውስጥ አንድ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲይን ጳጳስ ተገደሉ።

bishop_pardovese_insideIndependent Catholic News -Thursday, June 3, 2010 - እስከንደሩን በምትባለው አንዲት የቱርክ ከተማ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ሉዪጂ ፓዶቨዜ (63 ዓመት ዕድሜ)  በትላንትናው ዕለት በስለት ተወግተው መገደላቸው ታወቀ። በሜዲትራንያን ወደብ አጠገብ በሚገኘው የበጋ መኖሪያ ቤታቸው ጓሮ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ከአራት ዓመታት በላይ መኪና በማሽከርከር ያገለግላቸ በነበረው ሰው ጥቃቱ የተፈጸመባቸው መሆኑም ተገልጿል። የቱርክ ባለሥልጣናት ይህ ሁኔታ ጸረ ክርስቲያን ጥላቻዊ አቋምን ያለመ አይደለም ብለዋል። የቱርክ ፖሊስ ገዳዩን በእስር የያዙት ሲሆን ሰውየው ያልተረጋጋ አእምሮ ያለውና ከበድ ያለ ሥነ ልቦናዊ ችግር ውስጥ መሆኑን አሳውቀዋል።

ትውልደ ጣልያን የሆኑት አቡነ ፓዶቬዘ በአናቶሊያ የርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሐዋርያዊ እንደራሴና የቱርክ ጳጳሳት ጉባኤ ኀላፊ የነበሩ ሲሆን ከጥቃቱ በኋላ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል በመወሰድ ላይ ሳሉ ነበር ነፍሳቸው ያለፈችው። ር.ሊ.ጳ. በቆጵሮስ በሚያደርጉ ሐዋርያዊ ጉብኝት ለአጃቢነት ወደዚያው ሊያመሩ በዝግጅት ላይ ነበሩ።

ይህ ግድያ ምንም እንኳ ሃይማኖታዊ ምክንያት የሌለው ቢመስልም በቱርክ ውስጥ በቅርብ ዓመታት በክርስቲያኖች ላይ የተወሰኑ ጥቃቶች ተሰንዝረዋል። እ.ኤ.አ. በ2007 ዓ.ም. በአገሪቱ ምዕራብ በምትገኘው ኢዝሚር በምትባል ከተማ ልክ ቅዳሴ እንደጨረሱ አንድ የካቶሊክ ካህንን የ19 ዓመት ወጣት ወግቶ ያቆሰላቸው ሲሆን፤ በዚያኑ ዓመት በአንድ የመጽሐፍ ቅዱስ አሳታሚ ድርጅት ውስጥ የሚሠሩ ሦስት ክርስቲያኖች መገደላቸው ሲታወቅ በ2006 ዓ.ም. ደግሞ 16 ዓመት እድሜ ያለው ልጅ አባ አንድሬያ ሳንቶሮ የተባሉትን ካቶሊካዊ ካህን በጸሎት ላይ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሳሉ ከጀርባ በኩል ተኩሶ እንደገደላቸውም የሚታወቅ ነው።

Last Updated (Friday, 04 June 2010 22:31)

 

"ምእመናን ሁሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ጸሎት እንዲያደርጉ ለማሳሰብ እወዳለሁ፡፡" - አቡነ ብርሃነየሱስ ሊቀ ጳጳሳት ዘካቶሊካዊያን

 

"በመካከላቸው ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፡ በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ ሣይሆን፤ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ረብ
Abatachinበመመኘት ሣይሆን ጎብኙት" (1 ጴጥ. 5፡ 2)፡፡

 

መግቢያ

ከሁሉ አስቀድሜ ይህ ፕሮግራም በመዘጋጀቱ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ስም የተሰማኝን ደስታ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ "ከችግር መላቀቅ፤ የምግብ ዋስትና ማግኘት፤ ቋሚ ሥራ ማግኘት፤ ኃላፊነቶችን ያለ አድሎ መካፈል፤ ከጭቆና ሁሉ ነጻ መሆን፤ ሰብአዊ ክብሮችን ተከብሮ መኖር፤ የትምህርት ዕድል ማግኘት፤ የመኖር ዋስትናው ተጠብቆ መኖር፤ በአጠቃላይ የተሻለ ኑሮ መኖር" የኢትዮጵያ ሕዝቦች ምኞት ነው (የሕዝቦች እድገት 6)፡፡ "እያንዳንዱ ዜጋ መሪዎቹን መምረጥ የራሱ መብትና ኃላፊነት መሆኑን በማወቅ የመምረጥ መብቱን ተጠቅሞ ለሕዝቦች የጋር ጥቅም አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅበታል፤ ለሕዝብ አገልግሎት ራሳቸውን ለመሠዋት እጩ አድርገው የፖለቲካ ሸክም ለመሸከም የሚወዳደሩ ግለሰቦችን በአክብሮት እንመለከታለን" (ቤተክርስቲያን በዘመናችን 75)፡፡

1/ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት፡ በተቻለ መጠን በተለያዩ ፓርቲዎች መካከል ያሉ የምርጫ ልዩነቶችን ለማጥበብ የማያቋርጥ የመግባባት ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል ብለን እናምናለን፡፡

2/ የኃይል አጠቃቀምን ማስቀረት፡ በምርጫ ወቅትና በኋላም መራጮች ሆኑ ሥነ ሥርዓት አስከባሪዎች የኃይልና የአመጽ አጠቃቀምን ጨርሶ ማስቀረት፡፡ በአጠቃላይ የሰው ክቡርነት ከሀሳብ ልዩነታችን በላይ መሆኑን አውቀን ለሰላም የሚቻለውን ዋጋ መክፈል ተፈጥሮአዊ ግዴታችን ነው፡፡......

Last Updated (Friday, 04 June 2010 22:36)

 

እግዚአብሔርን በቍርጠኝነትና በታማኝነት ማገልግል ያስፈልጋል።

ቫቲካን ሬድዮ - ትናንትና እሁድ ረፋድ ላይ ቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይና በአከባቢው ያሉ ጐደናዎችን ያጥለቀለቀ ከሁለት መቶ ሺ በላይ የሚገመቱ ምእመናን በተገኙበት ቅዱስ አባታችን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ የንግሥተ ሰላም ጉባኤ አስተምህሮ አቅርበዋል። ምእመናኑ ከመላው ጣልያን የተሰበሰቡ ሆነው፣ ምክንያቱም በዚሁ ፈታኝ ጊዜ ምእመናን ቅዱስነታቸውን በጸሎትና በአካል እጐናቸው መሆናቸውን በማሳወቅ ድጋፋቸና አጋርነታቸውን ለመግለጥ መሆኑን ከቅድስት መንበር የወጣ መግለጫ አስታውቀዋል።
ቅዱስነታቸው የንግሥተ ሰማያት ጸሎት ከማሳረጋቸው በፊት ይህንን ትምህርት ሰጥተዋል፦

Last Updated (Saturday, 05 June 2010 19:45)

 
የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 6:
United States flag 33%United States (4)
Ethiopia flag 25%Ethiopia (3)
Russian Federation flag 17%Russian Federation (2)
Canada flag 8%Canada (1)
Moldova, Republic of flag 8%Moldova, Republic of (1)
Switzerland flag 8%Switzerland (1)
12 visits from 6 countries