ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ)

በቅርብ የተጨመሩ ጽሑፎች

የሆሳዕና ሃገረስብከት ምስረታ በታላቅ ድምቀት ተከበረ - የሃገረስብከቱ አዲስ ጳጳስ ቅብዓተ ጵጵስና ተከናወነ

የአዲሱ ሆሳዕና ሀገረስብከት ምስረታ ሚያዝያ 3 ቀን 2002 ዓ.ም በሆሳዕና ካቴድራል በታላቅ ድመቀት ተከብሮ ውሏል፡፡ የሃገረስብከቱ የመጀመሪያ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ወልደጊዮርጊስ ቅብዓተ ጵጵስናም በብፁዕ አቡነ ብርሀነየሱስ ሊቀጳጳሳት ካቶሊካውያን ዘኢትዮጵያ እጅ ተከናውኗል፡፡

abune woldeghiorghisበዕለቱ ብፁዕ ለቀጳጳሳት ጆርጅ ፓኒኩለም የቫቲካን አምባሳደር በኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት፣ክቡር አባ ፓየስ የአሜሲያ (የምስራቅ አፍሪካ ጳጳሳት ጉባዔ ጠቅላይ ጸሃፊ፣ ክቡር አባ ሐጎስ ሐይሽ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽ/ቤት ጠቅላይ ጸሐፊ፣ የተለያዩ ሃይማኖቶች ተወካዮች፣ ክቡር ዶ/ር ሺፈራው ተ/ማርያም የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር፣ ኩቡር አቶ መለሰ አለሙ የሃዲያ ዞን አስተዳዳሪ፣ አቶ ታደሰ ሮሞ የከምባታ ጠምባሮ ዞን ኣስተዳዳሪ፣ ከመላዋ ኢትዮጵያ፣ ከሆሳዕናና አካባቢዋ የተውጣጡ፣ ካህናት፣ ደናግልና ምዕመናን እንዲሁም የብፁዕነታቸው ቤተሰቦች ተገኝተዋል፡፡

በበዓሉ ላይም በሆሳዕናና በኣካባቢዋ የስብከተ ወንጌል እንዴት እንደተጀመረና እንደተስፋፋ የሚያብራራ አጭር ታሪካዊ ዘገባ ቀርበዋል፡፡...

Last Updated (Wednesday, 19 May 2010 21:42)

 

የሰሙነ ሕማማት ትርጉም


Passione-di-Cristo-Ecce_homo_bullas_copy

ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ጲላጦስም:- እነሆ ሰውዬው አላቸው። ዮሐ.19:5-6

አንድ አፈ ታሪክ ስለ ሁለት ወንድማማቾች ይተርካል። አንደኛው ጥሩ ምግባር የነበረው ሲሆን ሌላኛው ግን ክፋትን ያዘወትር ነበር። አንድ ቀን ክፋትን ያዘወትር የነበረው ወንድም ወደ ቤት በሩጫ መጣ ካባውም በደም ነጠብጣብ ተጨማልቆ ነበር። ቤት እንደገባም እየተረበሸ "አሁን አንድ የዋህ ሰውን ገደልኩ" በማለት ለወንድሙ ነገረው። ባለ መልካም ምግባር ወንድሙም "እንካ፤ አንተ የኔን ነጭ ካባ ልበስ፤ እኔ ደግሞ ያንተን እለብሳለሁ። ከዚያም አንተ ከዚህ አካባቢ ተሰወር" አለው። ወንድሙ እንዳለው አደረገና ገዳዩ ወደ ሌላ ቦታ ሄደ። ወዲያውም ወደዚያ ቤት ወንጀለኛውን ለማሰር የመጡት ሰዎች በደም የተጨማለቀ ካባ የለበሰውን ልጅ ወደ እስር ቤት ወሰዱት፤ ወዲያውም የሞት ፍርድ ተፈረደበት። ልክ ከመሞቱ በፊት ለገዳይ ወንድሙ መልእክት ላከለት፤ እንዲህም አለው "የሰጠሁህን ነጭ ካባ አስታውስ፤ እኔ አንተን ለማዳን ባንተ ምትክ መሞቴንም እንዳትረሳ"።

ባጭሩ ይህ ጌታችን ለኛ ያደረገውን ይነግረናል፦ የኛን የኃጢአት ካባ እሱ ለበሰው።

"በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕመማችንንም ተሸክሟል። በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን"....

 

ፕሬዚዳንት ግርማ የካሪታስ ኢንተርናሽናል ፕሬዚዳንትን አነጋገሩ

አዲስ አበባ, የካቲት 30 ቀን 2002 (አዲስ አበባ) - ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የካሪታስ ኢንተርናሽናል ፕሬዚዳንት ካርዲናል ኦስካር ሮድሪጌዝ ማራዲጋን በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

ካርዲናል ኦስካር ሮድሪገዝ ማራዲጋዝ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች እንዳስታወቁት ውይይቱ በዋናነት ያተኮረው ካሪታስ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ እያከናወነ ባላቸው የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ነበር፡፡ በዚህም ድርጅታቸው ኢትዮጵያ በማካሄድ ላይ ያለችውን ልማት የማገዝ ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል፡፡

በተለይም በትምህርት ዘርፍ ኢትዮጵያን ለማገዝ በሚያደርገው ጥረት በኢትዮጵያ የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ ለመገንባት በሂደት ላይ ይገኛል፡፡ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲን በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች የማስፋፋት ፍላጎት አለው ማለታቸውን የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብጹእ አቡነ ብርሃነየሱስ በበኩላቸው ካሪታስ ኢንተርናሽናል በመላው ዓለም በ162 አገሮች የልማትና የበጎ አድርጎት ተግባራት ላይ እንደሚሳተፍ ገልጸዋል፡፡

 
የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 9:
Ethiopia flag 24%Ethiopia (4)
Netherlands flag 18%Netherlands (3)
Unknown flag 18%Unknown (3)
Moldova, Republic of flag 12%Moldova, Republic of (2)
Germany flag 6%Germany (1)
Russian Federation flag 6%Russian Federation (1)
Switzerland flag 6%Switzerland (1)
United Kingdom flag 6%United Kingdom (1)
United States flag 6%United States (1)
17 visits from 9 countries