ንኡሳን ገጾች
Chaplet of Divine Mercy
Home (ቅድመ ገጽ) ዜናዎች ር.ሊ.ጳ. በሚስዮናዊው መገደል የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ

ር.ሊ.ጳ. በሚስዮናዊው መገደል የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ

VATICAN CITY, SEPT. 22, 2009 (Zenit.org).- ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው ባለፈው ቅዳሜ ብራዚል ውስጥ በተገደሉት ጣልያናዊ ሚስዮናዊ አባ ሩጄሮ ሩቮሌቶ ሞት ምክንያት የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ። ለማናዎስ ሊቀ ጳጳሳት ሉይስ ሶዋሬስ በላኩት የቴሌግራም ኀዘን መግለጫቸው ውስጥ ይህን "ሰላማዊ የወንጌል አገልጋይ ላይ ደስ የማይልና የጭካኔ ድርጊት" በጥብቅ በማውገዝ በጸሎት መንፈሳዊ አብሮነታቸውን ገልጸዋል።

አባ ሩቮሌቶ የተገደሉት በሰሜን ብራዚል

ማናዎስ በሚባል አካባቢ በሚያገለግሉበት ቁምስና በቅድስት ኤቬሊና ሲሆን ፖሊስ በመጀመሪያ ግድያውን ዘራፊዎች የፈጸሙት መሆኑን ቢጠቅስም ዛሬ የጣልያን ጳጳሳት ጉባኤ ዜና ወኪል ግን "ለረጅም ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ወንጀሎችን፣ የአደንዛዥ ዕፅና የሰውን ብዝበዛ ስለምትቃወም በማናዎስ አካባቢ ቀጣይ የሆነ ቤተ ክርስቲያንን የማስፈራራት ሁኔታዎች" መኖራቸውንና የኚህ ካህን መገደል እውነትም የዚህ ድርጊት ክፍል የመሆኑ ርግጠኝነት መጨመሩን ዘግቧል።

እ.ኤ.አ. ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ አባ ሩቮሌቶ "አደንዛዥ ዕፅና ሴትኛ አዳሪነት እንደ ኅብረተሰብ አደጋ" የገለጹባቸው ሰነዶችና ቃለ መጠይቆች እንዳሉም ታውቋል።

አባ ሩቮሌቶ በ1957 ዓ.ም. ጣልያን ቬኑስ አጠገብ ተወልደው በ1982 ዓ.ም. ሢመተ ክህነት የተቀበሉ ሲሆን ልኡከ ወንጌል ሆነው ወደ ብራዚል የተጓዙት ከስድስት ዓመታት በፊት ነበር።

Last Updated (Tuesday, 22 September 2009 22:36)

 

Add comment


የሳምንቱ መልእክት
"ለሰው ይኽን ያህል ታላቅ ክብር ለመስጠት ያነሳሳህ ምን ይሆን?...ወደር የሌለው ፍቅርህ እንደሆነ አይጠረጠርም! በፍቅሩ ተማርከሃል፤ በአውነትም በፍቅር ፈጥረኸዋል፤ በፍቅርም ዘላለማዊ መልካምነትህን የሚያጣጥም ስብእናን ለግሰኸዋል።" ቅድስት ካተሪና ዘሲየና
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ያን መዝሙሮች (ብዛት 110!)
ባለፉት 12 ሰዓታት የጎብኚዎች አገር
Top 9:
Ethiopia flag 24%Ethiopia (4)
Netherlands flag 18%Netherlands (3)
Unknown flag 18%Unknown (3)
Moldova, Republic of flag 12%Moldova, Republic of (2)
Germany flag 6%Germany (1)
Russian Federation flag 6%Russian Federation (1)
Switzerland flag 6%Switzerland (1)
United Kingdom flag 6%United Kingdom (1)
United States flag 6%United States (1)
17 visits from 9 countries