በኢራቅ የአናሳ ሃይማኖቶች ህልውና
ቫቲካን ሬድዮ - በኢራቅ የአናሳ ሃይማኖቶች ህልውና ላደጋ በመጋለጡ ምክንያት ዐቢይ የደኅንነት ጥበቃ እንደሚያስፈልገው የነዚህ አናሳ ሃይማኖቶች ተጠሪዎች የጸጥታ እና የደኅንነት ጥበቃን ጥሪ በማቅረብ በተለይ ደግሞ እ.ኤ.አ. ጥር ወር 2010 ዓ.ም. በአገሪቱ በሚካሄደው ሕዝባዊ መርጫ ወቅት ተገቢ የጸጥታ እና የደኅንነት ዋስትና ያገኙ ዘንድ ለአገሪቱ መንግሥት ጥሪ አስተላልፈዋል።
በኢራቅ አናሳ ሃይማኖቶች ለተለያዩ አደጋዎች በመጋለጣቸው ምክንያት መፍትሔው ራስን ለማዳን አገር ጥሎ መሰደድ ብቻ በመሆኑ የተያያዙት ስደት እንዲወገድ ከመንግሥት የጸጥታ እና የደህንነት ዋስትና መረጋገጥ ይኖርበታል። በኢራቅ አናሳ ከሚባሉት ሃይማኖቶች ውስጥ የእስልምና እና የክርስትናን አንዳንድ የእምነት ሥርዓቶችና ትምህርተ ሃይማኖትን በአንድ በማቀላቀል የሚያስተምር 300 ሺሕ ኢራቃውያን የሚከተሉት የሻባክ ሃይማኖት አንዱ ሲሆን፣ ሌላው የያዚዲ ሃይማኖት፣ የከለዳያን ሥርዓት የምትከተል ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን፣ የኦርቶዶስክ፣ የአሲሪያ፣ የአርመን፣ የአንግሊካን አቢያተ ክርስትያን የሚመለከት ጉዳይ ሲሆን፣ በኢራቅ በመንግሥት ደረጃ ሳይሆን በአቋም ስነ ሓሳብ የተደገፈ ጸረ የአናሳ ሃይማኖት ተግባር እየተስፋፋ መሆኑ ይነገራል።
Last Updated (Sunday, 31 January 2010 21:26)










