Font Size

Cpanel

Cistercians In Ethiopia - Ethiopian Catholic Church

You are here: Home ዜናዎች የሲታውያን ገዳም በኢትዮጵያ አዲስ መዋቅር አገኘ

የሲታውያን ገዳም በኢትዮጵያ አዲስ መዋቅር አገኘ

ከቅድስት መንበር (ቫቲካን) በተገኘው ፈቃድ መሠረት በሲታውያን ማኅበር ጠቅላይ አበምኔት ኀላፊነት በኢትዮጵያ የሚገኘው የሲታውያን ገዳም በአዲስ መልክ የተዋቀረ የመነኮሳን አስተዳደር ሂደት ጀመረ።

የሲታውያን ማኅበር ጠቅላይ አበምኔትና በዚህ ውሳኔ መሠረት የቅዱስ ዮሴፍ ገዳም ሾላ የበላይ ኀላፊ የሆኑት ማውሮ ጁዜፔ የማኅበሩ አስተዳዳሪ የሆኑትን አባ ሜይንራድ ጆዜፍ ቶማንን በመወከል ወደ ኢትዮጵያ ልከው ሰኔ ፭ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. በቅዱስ ዮሴፍ ገዳም ኀላፊ መነኮሳት አባቶች ተሰባስበው ውሳኔው ተግባራዊነቱን ጀምሯል። በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ የሚገኘው የቅዱስ ዮሴፍ ገዳም በክቡር አባ ባዘዘው (ወልደ ገብርኤል) ግዛው አባታዊ ኀላፊነት የተቀሩት ገዳማት ማእከል እንዲሆን ተደርጓል።

በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሳእናና በጎንደር የሚገኙት አራት የሲታውያን ገዳማት ስድስት በተመካሪ ደረጃ ላይ ያሉ መነኮሳትን አካትቶ በጠቅላላ ሠላሳ ሦስት መነኮሳት ያሉት ሲሆን በሥሩም ከመዋእለ ሕፃናት እስከ ተግባረ እድ ድረስ የሚያካትቱ በድምሩ ከአምስት ሺህ በላይ ተማሪዎችን የሚያስተናግዱ አብያተ ትምህርትን ያስተዳድራል፤ በቁምስና ደረጃም ሐዋርያዊ አገልግሎትን በሚመለከት በአራቱ ገዳማት አምስት ቁምስናዎችን የሚያገለግል ማኅበር ነው።

የሲታውያን ገዳም በኤርትራና በኢትዮጵያ እንዴት እንደተጀመረና ከ ፶፮ ዓመታት በፊት የመጀመርያው ገዳማችን የመንዲዳ ደብረ ጽንሰታ ዘሲታውያን ገዳም በምን ዓይነት ሁኔታ እንደተገደ ይበልጥ ለመረዳት ከታች ያለውን ገጽ እንዲጎበኙት እየጋበዝን ለሕይወታችን ቅድስናና ለሐዋርያዊ ሥራ አበርክቷችን በጸሎታችሁ ታስታውሱን ዘንድ አደራ እንላለን። http://www.ethiocist.org/index.php?option=com_content&;view=article&id=284&Itemid=669

በዚህ ጽሑፍ ክፍል ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ጽሑፋት

Other articles in ዜናዎች

የርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ 50ኛው የዓለም የጥሪ ጸሎት ቀን መልእክት 23 May 2013

የብፁዕ አቡነ ብርሃነየሱስ የ2005 ዓ.ም የጌታችን ትንሣኤ በዓል መልእክት 05 May 2013

የር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ ስብከት ዘሆሳዕና 2005 ዓ.ም. 28 April 2013

ቤተ ክርስቲያን ልጆችን የምታስተኛ ሞግዚት መሆን የለባትም! 19 April 2013

ካቶሊኮች የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን ደስታን በማሳየት ዓለምን አገልግሉ 11 April 2013

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ ከቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው ጋር ተገናኙ 27 March 2013

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ ማን ናቸው? 15 March 2013

"አዲስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አግኝተናል!" 13 March 2013

የቅዱስ አባታችን ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛውን ሕይወት የሚዳስስ ምርጥ ዝግጅት ያድምጡ 07 March 2013

ለር.ሊ.ጳ. ምርጫ ዝግጅት የመጀመሪያው የካርዲናሎች ጉባኤ ተካሄደ 05 March 2013

ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው የመንበረ ጴጥሮሳዊ አገልግሎታቸውን እንደሚያቋርጡ አስታወቁ። 11 February 2013

ሁላችን በጌታችን ፍቅር ልንሸነፍ ይገባናል! 07 January 2013

በሰባት ዓመቱ ሕፃን ጆሴፍ ራዚንገር /የአሁኑ ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው/ ለሕፃኑ ኢየሱስ የተጻፈ የገና ደብዳቤ 25 December 2012

ሢመተ ክህነት በገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን አዲስ አበባ 30 October 2012

መንፈሳዊ ምድረ በዳነት ባጠቃው ወቅታዊው ዓለም ዳግም ክርስቶስን ማወጅ 14 October 2012

የማይቃወመን እርሱ ከእኛ ጋር ነው! 05 October 2012

የእግዚአብሔር ሕዝብ በደም ትስስር በመሬትና በአገር ድንበር የቆመ አይደለም 01 October 2012

"ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች በአንድነት ቆመው አመፅ እንዲበቃ የሚያደርጉበት ጊዜው አሁን ነው!"፡ ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው በሊባኖስ 16 September 2012

ሊቀ ጳጳሳት ብ. አ. ብርሃነየሱስ የ2005 ዓ.ም ርእሰ ዐዉደ ዓመትን በማስመልከት ለምእመናን ያስተላለፉት መልእክት፡፡ 13 September 2012

ር.ሊ.ጳ. ቤኔዴክቶስ 16ኛው ለጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ህልፈት የኀዘን መግለጫ ላኩ። 22 August 2012

- Entire Category -

ተወራራሽ ርእሶች