Font Size

Cpanel

Cistercians In Ethiopia - Ethiopian Catholic Church

You are here: Home ዜናዎች የክህነት የብር ኢዮቤልዩና ሢመተ ዲቁና በማኅበረ ሲታውያን

የክህነት የብር ኢዮቤልዩና ሢመተ ዲቁና በማኅበረ ሲታውያን


ወንድም ዮሴፍ ፍቅረማርያም
ወደ መንዲዳ ዘርአ ምንኩስና የገቡት በ1989 ዓ.ም. ሲሆን ከዚያም በኋላ የተመክሮ ሕይወትን አድርገው ሕይወታቸውን እንደ ሲታዊ መነኩሴ በመሐላ ለእግዚአብሔር በመስጠት የፍልስፍናና የነገረ መለኮት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በመፈጸም ራሳቸውን ለክህነት አገልግሎት ሕይወት ሲያዘጋጁ ቆይተዋል፡፡ እነሆም በእግዚአብሔር ጸጋ በብፁእ አባታችን አቡነ ልሳነ ክርስቶስ ማቴዎስ እጅ ብዙ ካህናት፣ ደናግላን፣ ምእመናን፣ ቤተሰቦችና ወዳጆች በተገኙበት ሐምሌ 15 ቀን 2004 ዓ.ም ምስጢረ ዲቁና ተቀበሉ፡፡ መስዋዕተ ቅዳሴውን የመሩት ብፁዕ አባታችን አቡነ ልሳነ ክርስቶስ ማቴዎስ ቃለ እግዚአብሔር ባሰሙበት ወቅት ስለ ጥሪ አጽንዖት በመስጠት ‹‹ጥሪ የእግዚአብሔር ነው፡፡ እኛ ደግሞ የምንቀበለው እግዚአብሔርን በመታመን ነው እንጂ በራሳችን ኃይልና ዕውቀት በመተማመን አይደለም›› በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ መስዋዕተ ቅዳሴ ከተፈፀመ በኋላ ገዳሙ ባዘጋጀው የምሳ ግብዣ የዕለቱ መርኃ ግብር ተጠናቀቀ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ክቡር አባ አድነው ሎሬንሶ የክህነታቸው 25ኛ የብር ኢዮቤልዩ አከበሩ

ሐምሌ 19 ቀን 2004 ዓ.ም በሆሳዕና ቅድስት ሥላሴ ሲታውያን ገዳም ክቡር አባ ባዘዘው ግዛው የሲታውያን ገዳም ኃላፊ፣ ሌሎችም ብዙ ካህናት፣ ሲስተሮች ምእመናን፣ ቤተሰቦችና ወዳጆች በተገኙበት በድምቀት አከበሩ በዕለቱ መስዋዕተ ቅዳሴውን የመሩት ክቡር አባ አድነው ሎሬንሶ ባሰሙት ቃለ እግዚአብሔር ‹‹የዛሬው ቀን በሕይወቴ ትልቅ ቦታ የምሰጠው ነው፡ እለቱ የቅድስት ሐና አመታዊ ክብረ በዓል ሲሆን እኔ ደግሞ ያደግኩበት ቁምስና የተሰየመው በቅድስት ሐና ነው፡፡ በልጅነቴ እንደማንኛውም የገጠሪቱ የኢትዮጵያ ልጅ ወላጆቼን በእረኝነት አገለግል ነበር፡ ከእለታት አንድ ቀን ግን የተለየ ዜና ሰማሁኝ ይኸውም ከሰዳማ ቅድስት ሐና ቤተ ክርስቲያን እጅግ ርቆ በሚገኘው ዋሰራ ቅድስት ተሬዛ ቤተክርስቲያን ሃበሻ ካህናት ከመንዲዳ በመምጣት የመጀመሪያ ቅዳሴ ይቀድሳሉ የሚል ነበር፡፡ የተባለው ቀን ደግሞ ከብቶችን የመጠበቅ ተራ የእኔ ነበር፡፡ ስለዚህ በጠዋቱ ከብቶቹን ይዤ በመውጣት ሜዳ ላይ አንድ ጥላ ስር ስብስቤ ቅድስት ሃናን እባክሽን ዋስራ ደርሼ እስክመለስ ድረስ ክብቶቼን አደራ ብያት ወደ ዋሰራ ሄድኩኝ ስመለስም ከብቶቼን በሰላም አገኘኋቸው፡፡ እዛም ያየኋቸው የሲታውያን ካህናት እነ ነፍሰ ኄር አባ ሩፋኤል እና ቁጥራቸው የበዛ የዘርአ ምንኩስና ተማሪዎች ነጭና ጥቁር ለብሰው ሳይ ቅድስት ተሬዛን እንዲህ ስል ለመንኳት ‹‹እባክሽን እነዚህ ሰዎች ያሉበት ቦታ ሄጄ እንዳይ ፍቀጅልኝ፡፡ እነሆ ዛሬ ለእግዚአብሔር የሚሳነው የለምና የክህነቴን ማለትም የምዕመናን እረኛነቴን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ለማክበር በቃሁ፡፡ ክብር ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁን>> በማለት ስብከታቸውን ደመደሙ፡፡ ክቅዳሴ በኋላ በነበረውና ሁሉንም ባሳተፈው የቁርስ ግብዣ የዕለቱ መርኃ ግብር ተጠናቀቀ፡፡

ከመ በኩሉ ይሴባህ እግዚአብሔር!!

አባ ተሻለ ንማኒ/ዘሲታውያን/

በዚህ ጽሑፍ ክፍል ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ጽሑፋት

Other articles in ዜናዎች

የብፁዕ አቡነ ብርሃነየሱስ የ2005 ዓ.ም የጌታችን ትንሣኤ በዓል መልእክት 05 May 2013

የር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ ስብከት ዘሆሳዕና 2005 ዓ.ም. 28 April 2013

ቤተ ክርስቲያን ልጆችን የምታስተኛ ሞግዚት መሆን የለባትም! 19 April 2013

ካቶሊኮች የእግዚአብሔር ልጆች የመሆን ደስታን በማሳየት ዓለምን አገልግሉ 11 April 2013

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ ከቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው ጋር ተገናኙ 27 March 2013

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ ማን ናቸው? 15 March 2013

"አዲስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አግኝተናል!" 13 March 2013

የቅዱስ አባታችን ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛውን ሕይወት የሚዳስስ ምርጥ ዝግጅት ያድምጡ 07 March 2013

ለር.ሊ.ጳ. ምርጫ ዝግጅት የመጀመሪያው የካርዲናሎች ጉባኤ ተካሄደ 05 March 2013

ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው የመንበረ ጴጥሮሳዊ አገልግሎታቸውን እንደሚያቋርጡ አስታወቁ። 11 February 2013

ሁላችን በጌታችን ፍቅር ልንሸነፍ ይገባናል! 07 January 2013

በሰባት ዓመቱ ሕፃን ጆሴፍ ራዚንገር /የአሁኑ ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው/ ለሕፃኑ ኢየሱስ የተጻፈ የገና ደብዳቤ 25 December 2012

ሢመተ ክህነት በገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን አዲስ አበባ 30 October 2012

መንፈሳዊ ምድረ በዳነት ባጠቃው ወቅታዊው ዓለም ዳግም ክርስቶስን ማወጅ 14 October 2012

የማይቃወመን እርሱ ከእኛ ጋር ነው! 05 October 2012

የእግዚአብሔር ሕዝብ በደም ትስስር በመሬትና በአገር ድንበር የቆመ አይደለም 01 October 2012

"ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች በአንድነት ቆመው አመፅ እንዲበቃ የሚያደርጉበት ጊዜው አሁን ነው!"፡ ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው በሊባኖስ 16 September 2012

ሊቀ ጳጳሳት ብ. አ. ብርሃነየሱስ የ2005 ዓ.ም ርእሰ ዐዉደ ዓመትን በማስመልከት ለምእመናን ያስተላለፉት መልእክት፡፡ 13 September 2012

ር.ሊ.ጳ. ቤኔዴክቶስ 16ኛው ለጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ህልፈት የኀዘን መግለጫ ላኩ። 22 August 2012

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት ምክንያት የሐዘን መግለጫ መልእክት አስተላለፉ 17 August 2012

- Entire Category -