Map St Joseph Cistercians

Top Panel

7. ጤነኛ በራስ መተማመን

Jeremiah 2

7. ጤነኛ በራስ መተማመን
“ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። እኔም። ወዮ ጌታ እግዚአብሔር፥ እነሆ፥ ብላቴና ነኝና እናገር ዘንድ አላውቅም አልሁ። እግዚአብሔር ግን እንዲህ አለኝ። ወደምሰድድህ ሁሉ ዘንድ ትሄዳለህና፥ የማዝዝህንም ሁሉ ትናገራለህና። ብላቴና ነኝ አትበል።" ኤርምያሰ 1፡5-10፡፡

ኤርምያስ መናገር አልችልም ብሎ ደካማነቱን ከማወቁ የተነሣ በቅንነት ሲናገር የእግዚአብሔር መልስ ግን በኤርምያስ መተማመንን የያዘ ነበር፡፡ እኛ ስለእራሳችን የምናውቀውና እግዚአብሔር ስለኛ የሚያውቀው ምን ያህል የተራራቀ እንደሆነ እንረዳለን፡፡
በተጨማሪም በእኛ ዘንድ ደካማነት ሆኖ የሚታየው ለእግዚአብሔር ግን ቁጥር ውስጥ የማይገባና የማያሳስብ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ ጤነኛ በራስ መተማመን በእግዚአብሔር ፈት ከመቆም የሚመነጭ ነው፡፡ በራስ መተማመኔ የደከመ መስሎ ሲሰማኝ፣ ቀና ብዬ ለመሄድ ድፍረቱ ሲጎድለኝ ያደረግሁት ነገር ምን ነበር? ምን ዓይነት ዝንባሌ በውስጤ ሲቀሰቀስ ተሰማኝ?
ጤነኛ በራስ የመተማመን ስሜትስ ላይ እንዴት ልመለስ ቻልኩ?

በአባ ዳዊት ውብሸት

በድምፅ ለማዳመጥ ከታች ማጫወቻውን ይጫኑ (ንባብ  በዘማሪት ሕይወት መልአኩ)

 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት