Map St Joseph Cistercians

Top Panel

“ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው”

“ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው” መዝሙር 119፡1ዐ5መጽሐፍ ቅዱስ

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ  በ21ኛው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን ያስተማሩት ትምህርት

ከዚህ የሚከተለው ምክሬ በመዝሙር 1ዐ9፡1ዐ5 ላይ ሲሆን እርሱም ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው፤ የሚል ሲሆን ይህንን መልዕክት የተወደዱ ብጹዕ ጳጳስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ከዚህ በታች እንደሚከተለው አስቀምጠዋል፡፡ “እግዚአብሔርን በጸሎት የሚያመሰግን ሰው ቃሉ ለሕይወቱ ጨለማነቱን የሚያስወግድ ብርሃን ነው”፡፡

እግዚአብሔር እራሱን የሚገልፀው በሰዎች ታሪክ አማካኝነት ነው፤ እርሱ ለሰዎች ይናገራል፤ የሚናገረውም ቃሉ የመፍጠር ኃይል አለው፡፡ በዕብራይስጥ ቋንቋ “ዳባር” የሚለው ቃል ሁለት ትርጉም ያለው ሲሆን እርሱም የእግዚብሔር ቃል እና መፍጠር የሚል ነው፡፡ እግዚአብሔር የተናገረውን ይፈጥራል፤ የፈጠረውንም ይናገራል በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች የመሲሁን መምጣትና የአዲስ ኪዳን መቋቋም ሲያውጅ ቃል ስጋ በመልበስ እንደሆነ የገባውን የተስፋ ቃል በማፅናት ነው፡፡ ይህ አገላለጽ ዛሬ በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ሥጋ ለበሰ፤ ይህም ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነም ሁሉ ያለ እርሱ የሆነው አንድም የለም የሚል ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ፀሐፊዎችን የእምነት ልብ እንደከፈተ እንዲሁም ትርጉሙን ይረዱ ዘንድ የምዕመናንንም ልብ ይከፍታል፤ ይህም መንፈስ ቅዱስ በምስጢረ ቅዳሴ ካህናትን ኅብስቱንና ወይኑን ወደ ክርስቶስ ስጋና ደም የሚለውጡትን ቃላት ሲናገሩ በዚያ አለ፡፡ ምዕመናንም ሊኖሩና የሕይወታቸውን ጉዞ ሊጓዙ የሚችሉት በቃለ እግዚአብሔርና በክርስቶስ ሥጋና ደም ሲመገቡ ስለሆነ እነዚህ ሁለት ገበታዎች ሊለያዩ አይችሉም፡፡
ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛው

መንፈስ ቅዱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ፀሐፊዎችን የእምነት ልብ እንደከፈተ እንዲሁም ትርጉሙን ይረዱ ዘንድ የምዕመናንንም ልብ ይከፍታል፤ ይህም መንፈስ ቅዱስ በምስጢረ ቅዳሴ ካህናት ኅብስቱንና ወይኑን ወደ ክርስቶስ ስጋና ደም የሚለውጡትን ቃላት ሲናገሩ በዚያ አለ፡፡ ምዕመናንም ሊኖሩና የሕይወታቸውን ጉዞ ሊጓዙ የሚችሉት በቃለ እግዚአብሔርና በክርስቶስ ሥጋና ደም ሲመገቡ ስለሆነ እነዚህ ሁለት ገበታዎች ሊለያዩ አይችሉም፡፡ ሐዋሪያት የተቀበሉትና ለእኛም ያወረሱን የመዳን ቃል በጣም ውድ የሆነና የከበረ ስለሆነ በቤተክርስቲያንም ሆነ ከቤተክርስቲያን ውጪ በጥንቃቄ እንድንጠብቅና ይህ አካሄድ እንዳይጠፋ ኃላፊነትን እንውሰድ፡፡

የተወደዳችሁ ወጣቶች ሆይ የእግዚአብሔርን ቃልና ቤተክርስቲያናችሁን ውደዱ ይህንንም እንደ ትልቅ ሀብት በመቁጠር ትልቅ ዋጋ በመስጠት እንዴት ምስጋና ማቅረብ እንዳለባችሁ መልካምነትን ተማሩ፤ ፍቅርን በመከተል የእውነተኛ ደስታን መንገድ ለህዝብ በማሳየት ቤተክርስቲያንም ተልዕኮዋን ትወጣለች፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ለመኖር እውነተኛ ደስታን መፈለግና ማግኘት ቀላል አይደለም፤ ብዙውን ጊዜ የህዝብ አዝማሚያ በሀሳብ የገሃነም ምርኮኛ ነውና እነርሱ ነፃ የሆነም ሊመስላቸው ይችላሉ ነገር ግን ብዙውን ጊዜ በአሳሳች አስተሳሰባቸው ሲሄዱ የህይወታቸው ጉዞ ይጠፋባቸዋል፡፡ የተወደዱ አባታችን ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ እንደስቀመጡት የሰውን ነፃነት ወደ እውነተኛ ነፃነት እንድንመራ ያስፈልጋል፡፡ በጨለማ የሚጓዝ የዓለም ህዝብ ወደ ብርሃን እንዲወጣ ያስፈልጋልና ኢየሱስም ይህንን ጉዞ አስተምሮናል “እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእርግጥም ደቀ መዛሙትቴ ትሆናላችሁ፤ እውነትን ታውቃላችሁ፤ እውነትም ነፃ ያወጣችኋል” ዮሐ. 8፡3ዐ-31 እውነት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ነፃ ያደርገናል ሕይወታችንንም ወደ መልካም ይመራዋል፡፡

 

bibbia-copiaየተወደዳችሁ ወጣቶች ሆይ ብዙውን ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል በማሰላሰል መንፈስ ቅዱስ የልባችን አስተማሪ እንዲሆን አድርጉ በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር እንደሰው አለመሆኑን ትረዳላችሁ፡፡ እናንተ እራሳችሁ እውነተኛውን አምላክ መምሰልን ትማራላችሁ እንዲሁም የራሳችሁንና የዓለምን ታሪክ ታውቃላችሁ፡፡ ከልብ የሚመነጭ መሆኑንም ታያላችሁ በዚያን ሰዓት ከእውነት የመነጨ ሙሉ የልባችሁን ደስታ ትቀምሳላችሁ፤በዚህ ዓለም ስትጓዙ ፈተናዎች፣ ችግሮች፣ ህመምም ይደርስባችኋል፤ በዚያን ሰዓት መዝሙረ ዳዊት እንደሚያስቀምጠው “እግዚአብሔር ሆይ ስቃዬ እጅግ ከባድ ነው” ልትሉ ትችላላችሁ፤ /መዝ. 119፡1ዐ7 ነገር ግን በዚያን ሰዓት ከዳዊት ጋር የሚቀጥለውን ስንኝ መጨመርን አትርሱ፤ “በተስፋ ቃልህ መሰረት በህይወት አኑረኝ፣ ስላንተ ሕይወቴ ለማሳለፍ ዝግጁ ነኝ፤ ህግህንም አልረሳም” መዝ. 1ዐ9፡1ዐ7-1ዐ9 የሚወደኝ አምላክ በቃሉ ሁልጊዜ ከጐናችን በመሆኑ ይደግፈናል፤ የፍርሃትን ጨለማ ከልባችን ያስወግዳል በፈተና ጊዜ መንገዳችንን ያበራል፡፡


የዕብራውያን መልዕክት ፀሀፊ እንደፃፈው “በእርግጥም የእግዚአብሔር ቃል ህያውና የሚሰራ ነው ሁለት አፍ ካለው ሰይፍ ይልቅ ስለታም ነው ነፍስንና መንፈስን ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለያይ ድረስ የሚቆራርጥ ነው” ዕብራውያን 4፡12 የእግዚብሔር ቃል በጥንቃቄ ለማዳመጥ አስፈላጊና ለመንፈሳዊ ትግላችን እንደ መንፈሳዊ መሣሪያ መውሰድ ያስፈልጋል፣ ትግላችን ውጤታማ የሚሆነው ስንማርና ስንታዘዝለት ነው፡፡ በትምህርተ ክርስቶሳችንም እንደተገለፀው “ለመጽሐፍ ቅዱስ መታዘዝ ማለት ማዳመጥና ቃሉን በህይወታችን መተርጐም ነው” ምክንያቱም እውነት በእግዚአብሔር የተሰጠ ስጦታ ነው፡፡ እርሱ ራሱ እውነት ነው፤ አብርሃምም የእግዚብሔርን ቃል በመስማት ታዘዘለት፣ ሰለሞንም እርሱ እንዳሳየው ጥልቅ በሆነው ስሜትና ጥበብ ባለው ቃል ይገልፀዋል “ምን እንድሰጥህ ትፈልጋለህ?” ተብሎ በተጠየቀ ጊዜ ጠቢብ ንጉስ “ለእኔ ለአገልጋይህ የመረዳት ልብ ስጠኝ” አለው 1ኛ ነገስት 3፡5-9 የመረዳት ልብ ለማግኘት ማለት ልቡን ለማዳመጥ ማሰልጠን ነው፡፡ ይህም የሚገኘው የእግዚአብሔር ቃል በዘላቂና በጥልቀት በማሰላሰልና በተጠናከረ ሁኔታ በትዕዛዙ መሰረት በመቀጠል ነው፡፡

 

የተወደዳችሁ ወጣቶች አሁን የማስገነዝባችሁ እናንተ ራሳችሁን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እንድታለማምዱ ከእጃችሁ መጽሐፍ ቅዱስ እንዳይለይና የግላችሁ ዕቃ አድርጋችሁ በመንገዱ እንድትከተሉ ነው፤ እርሱንም በማንበብ ክርስቶስን ታውቃላችሁ በዚህ ረገድ ቅዱስ ሄሮኒሞስ እንደሚለው “መጽሐፍ ቅዱስን አለማወቅ ክርስቶስን አለማወቅ ነው”

ቃለ እግዚአብሔርን ለማጥናትና ለመቅመስ ልዩ ስጦታ አለ እርሱም ንባበ መለኮት ይባላል፡፡ እርሱንም እናንተ ደረጃ በደረጃ በመውሰድ የሕይወታችሁን መንፈሳዊ ጉዞ ያሳድጋል፡፡

  • 1ኛ ደረጃ ማንበብ፡- ማንበብ ማለት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ በመውሰድ በድጋሚ በጥልቅ ማንበብና ዋናውን መልዕክት ማጥናት ነው፡፡
  • 2ኛ ደረጃ ማሰላሰል፡- በማሰላሰል ጊዜ በስሜት ነፍስን ወደ እግዚአብሔር በመመለስ ቃሉ ዛሬ ለእኔ ምን ይላል የምንልበት ጊዜ ነው፡፡
  • 3ኛ ደረጃ መጸለይ፡- መጸለይ ማለት በቀጥታ ከእግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርበት ደረጃ ነው፡፡
  • 4ኛ ደረጃ መመሰጥ፡- በዚህ ደረጃ ጊዜ ልባችንን ለጌታ መምጣት የምንከፍትበት ጊዜ ነው፡፡ ቃሉም “ሌሊቱ እስኪነጋና የንጋት ኮከብ በልባችን እስከበራ ድረስ በጨለማ እንደሚበራ መብራት አድርጋችሁ ብትጠነቀቁለት መልካም ነው” 2ኛ ጴጥሮስ 1፡19
  • 5ኛ ደረጃ ማካፈል፡- ቃሉን ማንበብ ማጠናትና ማሰላሰለ ከዚያም ወደ ሕይወት ማስገባት በክርስቶስ ፅኑ ወደ ሆነው እምነት ይጋብዘናል እርሱ ማለት ደግሞ ማካፈል ነው፡፡

ቅድስ ያዕቆብ እንደለው “ቃሉን በሥራ ላይ የምታውሉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያታለላችሁ ሰሚዎች ብቻ አትሁኑ ቃሉን ሰምቶ በስራ ላይ የማያውለው ሰው የተፈጥሮ ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ ሰው ነው ምክንያቱም ይህ ሰው ፊቱን በመስታወት ካየ በኋላ ይሄዳል እንዴት እንደሆነም ወዲያውኑ ይረሳዋል፡፡ ነገር ግን ነፃ የሚያወጣውን ፍፁም ሕግ ተመልክቶ በእርሱ የሚፀና እርሱንም ሰምቶ መርሳት ሳይሆን በሥራ ላይ የሚያውለው ሰው በሥራው የተባረከ ነው” ያዕቆብ 1፡ 22-25 “ቃሉን ሰምቶ በስራ ላይ የሚያውል ሁሉ ቤቱን በአለት ላይ የሰራውን ብልህ ሰው ይመስላል ማንም ቃሌን የሚሰና በስራ ላይ የሚያውለው ኢየሱስ እንዳለው ልክ በአለት ላይ ገንብቷል” ማቴዎስ 7፡24 ኃይለኛ ነፋስ ቢመጣ እንኳን አይወድቅም፡፡

ሕይወታችሁን በክርስቶስ ላይ መገንባት ቃሉን በደስታ መቀበልና በተግባር ላይ ማዋል የሕይወታችሁ እቅድ ይሁን፡፡ ሕይወታችሁን በክርስቶስ ላይ መገንባት በዚህ ዓለም ለሚነሱ ችግሮች ራሳችሁን እንደ አዲስ ሐዋሪያት በማዘጋጀትና በስራ በመተግበር ጊዜያችሁን በመጠቀም ወንጌልን በጥልቀትና በስፋት ለማሰራጨት ችሎታ ያላችሁ እንድትሆኑ ይረዳችኋል፡፡ ክርስቶስም የሚጠይቃችሁ ይህንኑ ነው፣ ቤተክርስቲያንም የምትጋብዛችሁ ይህንን ለዓለም በማስገንዘብ እንድትጠብቁ ነው፡፡ ኢየሱስ ከጠራችሁ አትፍሩ፣ በተለይም እሱን እንድትከተሉት የሚጠይቃችሁ ሕይወታችሁን እንድትሰጡ ወይም በክህነት እንድታገለግሉ ሲጠራችሁ አትፍሩ በእርሱም ታመኑ አያሳፍራችሁም፡፡

የተወደዳችሁ ወጣቶች ሆይ አሁን በዚህ ሰዓት የእግዚአብሔርን ድምፅ በመስማትና መንፈስ ቅዱስን በመለመን ምስክሮች ትሆኑ ዘንድ ያለምንም ፍርሃት እስከ ዓለም ፍፃሜ ወንጌልን እንድታውጁ እጋብዛችኋለሁ፡፡ እመቤታችን ማርያም ከሐዋሪያት ጋር በመንፈስ ቅዱስን ትጠብቅ ነበር ቃሉን በልቧ በማሰላሰልና በሙሉ ሕይወቷ በመፈፀም ትኖር ነበር የእግዚብሔርን መኖር በግልፅ ልታውጅ በመታዘዝና በእምነት ተነሳሳች፣ በእምነቷና በጸናው ተበስፋዋ ሳትሰለች የእግዚብሔርን ቃል ታሰላስል ነበር፣ በአንድነት በጸሎት እንድንተጋ ከሙሉ ልቤ በአባታዊ ቡራኬዬ እባርካችኋለሁ፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት