እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በአዲስ አበባ ካቶሊካዊ ሰበካ የሐዋርያዊ ሥራ ማስተባበሪያ ቢሮ ኮሚኒኬሽንና ኦዲዮ ቪዥዋል የሚዘጋጅ በእሑድ የወንጌል ንባባት ላይ ማስተንተኛ።

ሰንበት ዘብርሃን 2005 ዓ.ም.

ሰንበት ዘብርሃን 2005 ዓ.ም.

መዝሙር፡ አቅዲሙ ነገረ በኦሪት ከመ ይመጽእ ወልድ በስብሓት. . . . ።

ንባባት፡ ፍሊጲስዩስ 1፡4~11፥ 2ጴጥ 3፡8~14፥ ግ.ሓ. 26፡12~19 ሉቃስ 3፡1~6

ምስባክ፡ ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ፥ እማንቱ ይምርሓኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ፥ ወውስተ አብያቲከ እግዚኦ። መዝ. 43፡3~4 በዛሬው ሰንበት ከሚነበበው ወንጌል ኃይለ ቃል አድርገን የምንወስደው «ወደ ወገኖቹ መጣ፤ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም ፤» የሚለውን ነው (ዮሐ፡ 1፡11)፡፡

Calvaryእዚህ ላይ መነሳት ከሚችሉት መሠረታዊ ጥያቄዎች መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ይሆናሉ፡ «እነማን ናቸው ወገኖቹ...ይህን ያህል እምነት የተጣለባቸው? ይህ ክብር የተሰጣቸው? ምናልባት በስልጣን ከፍ ያሉ ወይም በሀብታቸው ዓለም በልዩ መዝገብ ላይ ያሰፈረቻቸው ናቸው? ምናልባት በመገናኛ ብዙኃን ቀን ከሌሊት የሚወራላቸው ይሆኑ የእርሱ ወገኖች?» መጽሐፍ ግን የክርሰቶስን ወገኖች «ታናናሽ» ብሎ ነው የሚጠራቸው፡፡ የክርስቶስ ወገኖች እርሱን በቅን እና በትሁት ልብ የሚፈልጉት ናቸው፣ ምክንያቱም በወንጌሉ መሰረት ግን የእግዚአብሔር ወገን ነኝ ያለ ሁሉ እውነትም ወገን ሆኖ ክርሰቶስን የተቀበለ አልተገኘም በዘመኑ፡፡ ስለዚህ በተስፋው መሠረት ቃል የተገባለት እና የተመረጠው ሕዝብ ሳይሆን ለአሕዛብ ሆነ፣ መዝሙረኛው ዳዊት «የማላውቀው ሕዝብ ተገዛልኝ...ትዕዛዜን እንደሰሙ ይታዘዙልኛል» እንዳለው (መዝ፡ 18፡43)፡፡ የመዳኛው ቀን መምጣቱን መሲሕም በመካከሉ መቆሙን ያላወቀው፣ የተመረጠ ሕዝብ በመሆኑ ብቻ ይታበይ የነበረው ግን ዐይኑም ልቡም ታውሮ ነበርና ወገኔ ብሎ የመጣውን አምላክ ሊቀበለው አልቻለም፡፡ ክርሰቶስም ይህን የመዳኑን ጊዜ ላላወቀው ሕዝብና ከተማ አለቀሰለት (ሉቃ፡ 19፡41-44)፡፡ ልበ ትሁታን ግን አንዴ ሲያዩት፣ የአፉን ትምህርት ሲሰሙ፣ የእጁን ድንቅ ስራዎች ሲመለከቱ በአግራሞት ተሞሉ፣ ጨለማቸው በራላቸው፤ ቅ. ጳውሎስ «እስራኤል አጥብቀው የፈለጉትን አላገኙትም፣ የተመረጡት ግን አገኙት፣ የቀሩት ልባቸው ደነደነ» እንዳለው (ሮሜ 11፡7)፡፡

የዛሬው ወንጌል «ሁሉ በርሱ ተፈጠረ» ይላል (ዮሐ 1፡3)፡፡ ከዚህ የምንማረው ደግሞ ሁሉ በክርስቶስ ተፈጥሮ ሳለ ፍጡር ግን ከዳተኛ ሆነ፤ ፈጣሪውንም ጠንቅቆ ባለማወቁ አምላኩ በጎበኘው ጊዜ ወደ ልቡ ሳያስገባው፣ ሳይቀበለው ቀረ፣ በፈጣሪው ላይም ልቡን አሸፈተ፡፡ ነገር ግን በፍጥረታችን ደካማ፣ አንዳንዴም አስቸጋሪ ብንሆንም ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን የማይጠላ አምላክ ነውና «ወገኖቼ» ብሎ መምጣቱን አያቋርጥም፡፡ ከሰው የሚጠበቀው ደግሞ በበር ቆሞ የሚያንኳኳውን እና ብርሃን የሆነውን ወደ ልቡ ማሰገባት ነው (ራዕ 3፡20)፡፡ ለእግዚአብሔር ጥሪ ጆሮውንም ልቡንም የሚዘጋ ግን ለመጥፋቱ ኃላፊነቱን ይወስዳል፡፡ «ብርሃን ወደ ዓለም መጣ» እንዲል መዝሙሩ፣ ይህን ብርሃን መጥራት፣ መጋበዝ፣ በርሱም መመላለስና መኖር ያስፈልጋል፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን ወይም ማመናችን ወደዚህ ብርሃን ካላቀረበን ወይም የክርሰቶስ ወገናዊነታችንን ካላመለከተ ጎዶሎ እምነት ነው፤ የምንመላለሰውም በደመዘዘ ብርሃን ውስጥ ነው፡፡

እንግዲህ ክርስትናችን የሰንበት ወይም የዓመት በዓል ክርስትና፣ የአጋጣሚ ክርስትና እንዳይሆን ብርሃን እና የብርሃንም አባት የሆነው ክርስቶስ ጸጋውን ያብዛልን፤ የጨለማን ሥራ አስወግደን በብርሃን እንድንመላለስ የእርሱም ወገኖች እንድንሆን ያበቃን ዘንድ የአምላካችን መልካም ፍቃዱ ይሁንልን! አሜን!

አባ ዳዊት ወርቁ

የካፑቺን ታናናሽ ወንድሞች ማኅበር

Write comment (0 Comments)

ግንቦት 26 2004 ዓ.ም - ቡሩክ በዓል ጰራቅሊጦስ

ግንቦት 26 2004 ዓ.ም - ቡሩክ በዓል ጰራቅሊጦስ

1ቆሮ 15፡ 2ዐ-34 1ጴጥ 1፡1-12 ዮሐንስ 2ዐ፡1-23

ሁለት ነጫጭ ልብስ የለበሱ መላእክት ጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በተቀበረበት መቃብር እግርጌና እራስጌ ተቀምጠው አንቺ ሴት ስለምን ታለቅሻለሽ ብለው ማርያምን ይቀይቋታል፤ ጌታዬን ወስደውታል ወዴት እንዳኖሩት አላውቅም ብላም ትመልስላቸዋለች ያንጊዜ ነበር ኢየሱስ "ማርያም" ብሎ ጠራት እርሷም ዘወር ብላ ረቡኒ በዕብራይስጥ መምህር ማለት ነው" ነጫጭ ልብስ የለበሱት መላእክት እንደ አለባበሳቸው ደስታን አብሳሪ ብርሃንን ፈንጣቂ ተስፋን የሚገልጥ መልዕክትን የያዙ ናቸው፡፡ በደስታ ተሞልተው ደስታን የሚያበስሩ ዛሬም መላዕክቱ ደስታን የሚያበስሯት መግደላዊት ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰባት አጋንንት ያወጣላትንና ከስቃይ ካዳናት በኋላ የክርስቶስ አገልጋይ የነበቀበሩ ምና የመረች ስትሆን የስቅለስክር የሆነች እንዲሁም ከሞት ከተነሳ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ክርስቶስ የታያት ትልቅ አገልጋይ ነበረች፡፡ የዛሬውም ወንጌል ይህንኑ በሰፊው ያሳየናል፡፡ ማርያም መግደላዊት የተደረገላትን ውለታ ቆጥራ የክርስቶስ አልጋይ ነበረች እስከመስቀሉና ሕማማቱን ተካፍላለች፡፡ ከእነዚህ አገልጋዮች ዛሬ እኛ ልንማር የሚገባን ብዙ ነገሮች አሉን፡፡ ማርያም መግደላዊት ከጌታችን ከመድኃኒታችን ስር ስር እየተከተለች ስቃዩን ሁሉ ተካፋይ ነበረች፡፡ ዛሬ እኛስ የወንድሞቻችን ችግር፣ ሐዘን፣ ሕመም እንካፈላለን ዋናው ከክርስቶስ ጋር መሆንና የክርስቶስን ሕይወት ተካፋይ ከሆንን የነዚህን የወንድሞቻችንን ነገሮች ሁሉ መሸከም ይገባናል፡፡

ምንባቡ ስለ ምን ይናገራል?

እንደ ማርያም መግደላዊት ተደረገልንን እናውቃለን?

Write comment (0 Comments)

ግንቦት 12 ቀን /2004 ዓ.ም - "ከነዚህ ይልቅ ትወደኛለህ?"

ግንቦት 12 ቀን /2004 ዓ.ም -  "ከነዚህ ይልቅ ትወደኛለህ?"

ሮሜ 6፡1-14 1ጴጥ 4 ፡1-11 ዮሐ 21፡12-25

የምህረት አምላክ የእግዚአብሔር የአዳኛችን የኢየሱስ ክርስቶስ በፀጋው የሚመራን የመንፈስ ቅዱስ ሰላም እና ጥበቃ ይብዛልን፡፡ከዚህ ከጳዉሎስ መልዕክት የምንረዳዉ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐጢያት ነፃ በማዉጣት ክፉን በማሸንፍ፣ ሕይወት የሰጠ እርሱ ነዉ፡፡በመንፈስ ቅዱስ ህይወት እንድናገኝ ሙሉ እምነት እንዲኖረን ያስፈልጋል፡፤ምንባቦች እንድናስብ ይጋብዘናል፡፡ ከክርስቶስ ጋር ያለን ህብረት ያመለክተናል፡፡ ጥምቀት የኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ተካፋይ እንደሆንንና በትንሳኤዉም ተካፋይ መሆናችንን ያመለክታል፡፡ ሐዋርያዉ ጴጥሮስ እንደ ስጋ ፍቃዳችን ሳይሆን በእግዚአብሔር ፍቃድ ዉስጥ እንድንመላለስ ይጋብዘናል፡፡ህብረታችን ፣ኑሯችን፣ ሁለንተናችንን ህይወትን በሰጠን በክርስቶስ ኢየሱስ እንዲመራ እና መገዛታችን ለክፋት እንዳይሆን ያስገነዝበናል፡፡በዮሐ. 21-15 ጀምሮ የእግዚአብሔርን ቃል ስናነብ ጴጥሮስ በክርሰቶስ ኢየሱስ የወንጌል አምባሳደር ሆኖ ሲገኝም እንመለከታለን፡፡በክርስትና ህይወት ዉስጥ ክርስቶስ ህይወታችንን እንድንፈትሽ ይጋብዘናል፡፡ እንድንታመን የእሱ አገልጋይ እንድንሆንም እንጋበዛለን፡፡ ጴጥሮስ የቱንም ያህል ደካማ ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ ግን ሀላፊነት ተሰጠዉ መንጋን የመጠበቅ፡፡ስለዚህ ከዚህ ቃል የምንረዳዉ ክፋትን በእረሱ በመታመን በማሸነፍ ፍቃዳችንን ለእርሱ በማስገዛት በእምነት ፀንተን ለሌሎች ምስክሮቹ እንድንሆን እንጋበዛለን፡፡እንዲሁም የእግ/ርን መመልከት በእርሱም ፍቃድ መመላለስ ለቅድስና የተጠራንበትን ህይወት እንድንኖር ብርታት ይሆነናል፡፡በመጨረሻ ቃሉን ለህይወታችን መመሪያ በማድረግ በፀሎት ክፋትን በማሸነፍ የተሻለዉን እና የሚበልጠዉን የእግ/ርን በረከት ለመቀበል እንድንችል መበርታት ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ ቃል የምንረዳዉ ክፋትን በእረሱ በመታመን በማሸነፍ ፍቃዳችንን ለእርሱ በማስገዛት በእምነት ፀንተን ለሌሎች ምስክሮቹ እንድንሆን እንጋበዛለን፡፡እንዲሁም የእግዚአብሔርን መመልከት በእርሱም ፍቃድ መመላለስ ለቅድስና የተጠራንበትን ህይወት እንድንኖር ብርታት ይሆነናል፡፡በመጨረም ቃሉን ለህይወታችን መመሪያ በማድረግ በፀሎት ክፋትን በማሸነፍ የተሻለዉን እና የሚበልጠዉን የእግ/ርን በረከት ለመቀበል እንድንችል መበርታት ያስፈልጋል፡፡

ምንባቡ ስለምን ያናገራል?

ሙሉ እምነት አለን? ሙሉ እምነት እንዲኖረን ምን ማድረግ አለብን ?

Write comment (0 Comments)

ግንቦት 19 ቀን 2004 - እጆቹን አንስቶ ባረካቸው የዕርገት በዓል ይሁንልን

ግንቦት 19 ቀን 2004 - እጆቹን አንስቶ ባረካቸው የዕርገት በዓል ይሁንልን

ሮሜ 1ዐ፡1-13 1ጴጥ 3፡13-22 ሉቃስ 24፡ 45-53

ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ አምስት ኪ.ሜ ርቆ ከደብረዘይት ወዲያ የሚገኝ መንደር የማርያም፣ የማርታና የአልአዛር እንዲሁም የለምጻሙ የስምኦን መኖሪያ የነበረና ከዮርዳኖስ በስተምስራቅ የሚገኝ መንደር ነው ቢታንያ የስሙም ትርጓሜ የበለስ ቤት ማለት ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በኋላ ሐዋርያቱን ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ አግኝቷቸው በመካከላቸው በመሆን ከእነሱ ጋር በሕይወት እያለ በነብያት በሙሴ ሕግና በመዝሙራት ስለእርሱ ይነገር የበረውን እናም እርሱ የነገራቸውን ሁሉ አእምሯቸውን ከፍቶላቸው እንዲያስተውሉ አድርጓቸው ነበር፡፡ ቃሉን የሚያከብር አምላክ ቃሉን ጠብቆ የራሱን ቃል አከበረው ስለራሱ የተነገሩትን ሁሉ ደግሞ ደጋግሞ አደረገው ሰዎች ነንና ያየነውን የሰማነውን ለማመን እንቸገራለን ግን ለምን? ማመን ለምን ይሳነናል? በእርግጥ የእግዚአብሔር ድንቀ ስራዎች ከሰዎች እምነት በላይ ድንቅ ነው፡፡ ስለዚህ ይመስላል ሰዎች አድራጊው አምላክ የሚያደርጋቸው ድንቅ ነገሮች በሰው ልጅ አእምሮ ሊገመት የሚችል ባለመሆኑ ማመን ያዳግተናል ምንም እንኳን የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አምሳያ የተፈጠረ ቢሆንም አእምሮ ግን የሰው ልጅ ይለያል፡፡ ስለዚህ ቀድሞ ሐዋርያቶች በዓይናቸው እንዳዩት ሁሉ ዛሬም እኛ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እያየን ስለሆነ አምነን ስንቀበል በተግባር ስንፈጽመው ጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያቶቹን እጆቹን አንስቶ ባርኳቸው ወደ ሰማይ እንዳረገ ሁሉ እኛንም በመጨረሻው ወቅት ይባርከናል፡፡

• ምንባቡ ስለምን ይናገራል?

• በእምነታችን ምን ያህል ጠንካሮች ነን?

• በእምነታችን ጠንካሮች ለመሆን ምን ማድረግ ይገባናል?

Write comment (0 Comments)

ግንቦት 5 2ዐዐ4 - መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉት

ግንቦት 5 2ዐዐ4 - መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉት

ሮሜ 4፡13-24  ራዕይ 2ዐ፡ 1-6 እና 11-15    ዮሐ 21፡ 1-41

ምህረት አምላክ የእግዚአብሔር የአዳኛችን የኢየሱስ ክርስቶስ በፀጋው የሚመራን የመንፈስ ቅዱስ ሰላም እና ጥበቃ ይብዛልን፡፡እግዚአብሔር ለአብርሃም ታላቅ ነገርን ያደረገለት በእርሱ ላይ ባለዉ እምነት ነዉ፡፡ ያም የገባለትን ቃልኪዳን ለመፈጸም የመሲሑን መምጣት በተስፋ መጠበቅ ያስፈልገውም ነበር፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን የሚችል አምላክ እንደሆነ በይስሐቅ መወለድ ማየት እንችላለን፡፡ዘፍ 17፡ 17-18 አብርሐም ከነበረዉ ችግሩ ይልቅ እግዚአብሔርና የተሰጠዉን ተስፋ ይመለከታል፡፡ የአብርሐም እምነት በይገባኛል የተሞላ ሳይሆን በተስፋ ሰጪዉ አምላክ ክብርን በመስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ሺ ዓመት መጨረሻ የሌለዉ ንግስና ያመለክታል፡፡ የክርስቶስን ዘላለማዊ ንጉስነት እንድንመለከተዉ ይጋብዘናል፡፡ በወንጌሉ ሐዋርያት የሰጣቸዉን የተስፋ ቃል በመዘንጋት ተስፋ ቆርጠዉ ወደነበሩበት ታሪካቸዉ መመለሳቸዉን እና ዳግም ክርስቶስ በህይወታቸዉ ተገልጦ ‹‹ ጌታ እኮ ነዉ›› በማለት አይነ ልቦናቸዉ እንደተገለጠ በቃሉ እናገኛለን፡፡

1. ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል የሚያስተምረን በእኛ የጊዜ ቀመር ሳይሆን እንደፈቃዱ በታሪካችን ዉስጥ ያልነበረንን፡ ተስፋ የቆረጥንበትን በመፈፀም ታላቅ ነገርን በህይወታችን የሚያደርግ አምላክ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡

2. ክርስቶስ አምላካችን ፍጹም አምላክ እንደሆነ ንግስናዉም መጨረሻ የሌለዉ ልዑል የሆነ አልፋ ኦሜጋ እንደሆነ መገንዘብ ይጠበቅብናል፡፡

3. አይነ ልቦናችንን ከፍተን በቃሉ በመኖር ተስፋችንን ማለምለም ያስፈልጋል፡፡

ስለዚህ በእምነት መጽናት ፤በተስፋዉ ቃል መኖር እራሳችንን ኑሯችንን ለእርሱ መስጠት ስንችል እግዚአብሔር በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ታሪካችን ይገባል፡፡ ታላቅ ነገርን ያደርግልናል፡፡ በረከትና ዋጋዉን ያበዛል፣ ዘመናችን ልክ እንደ አብርሃም ይባረካል፡፡የበረከት አምላክ የበረከቱ ተካፈይ ያድርገን አሜን፡፡

• ምንባቡ ስለምን ይናገራል ?

• እኛስ ዘመናችንን እንዴት እናየዋለን ?

Write comment (0 Comments)

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት