እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ጥቅሶች

"ሰው በሕይወቱ እግዚአብሔር እንደሌለ ሆኖ ከኖረ፤ የእግዚአብሔርን ብቻ ሳይሆን የራሱንም ሆነ የዓለምን ምንነት ትርጉም ያጣል"

ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ "የሕይወት ብሥራት" በሚለው መልክታቸው ቁ.24

 

ቀጣይ ፈተና

"ፍቅር በቀጣይነት ከእግዚአብሔር ወደኛ የሚላክ ተፈታታኝ ጥያቄ ነው።" - (ከኛ መልስን በመሻት እግዚአብሔር አሁንም አሁንም እወድሃለሁ/እወድሻለሁ ይለናል)

 

ነጻነት ዒላማውን ሲስት

ነጻነት ዓላማ ከሌለው፣ በሰው ልጆች ልብ ውስጥ የተቀረጸውን ሕግ ለማወቅም ካልተመኘና የኅሊናንም ድምጽ መስማት ከተሳነው፣ ኅብረተሰብንና የሰው ልጅን ማጥፋት ይጀምራል። 

 

ባዶ ድኻ፤ ሙሉ ሀብታም የለም!

አንድ ሰው የመጨረሻ ድኻ ቢሆንም እንኳ ለሌላ ሊሰጥ የሚችለው ነገር አለው፤ እንዲሁም ሌላውም በጣም የተትረፈረፈው ሀብታም ቢሆንም ከሌላ ሰው መቀበል የሚያስፈልገው ነገር አለ።

 

የዓለም ዘግናኙ እስር ቤት - የራስ ልብ

ከእስር ቤቶች ሁሉ ዘግናኙ እስር ቤት በተዘጋ ልብ ውስጥ መኖር ነው።

 

የትንሣኤ ሕዝብ!

ራሳችሁን ለተስፋ ቁርጠት አሳልፋችሁ አትስጡ! እኛ የትንሣኤ ሕዝብ ነን፤ ዝማሬያችንም ሃሌሉያ ነው!

 

ነጻነት ኀላፊነት ነው

·በኃይልና ዓመፅ ለአንድ ኅብረተሰብ ፍትሕን ማምጣት አይቻልም፤ ዓመፅ ራሱ አመጣለሁ የሚለውን ፍትሕ ያጠፋዋል።

·ነጻነት ማለት የፈለግነውን ማድረግ የመቻል መብት ማለት ሳይሆን፤ ማድረግ የሚገባንን ማድረግ የመቻል መብት ነው።

·እውነተኛ ቅድስና ማለት ከዓለም መሸሽ ማለት አይደልም፤ ነገር ግን ወንጌልን በየአንዳንዷ የዕለታዊ ሕይወታችን ውስጥ በቤተሰብ፣ በትምህርት ቤት፣ በሥራ ቦታና በኅብረተሰብ ውስጥ ለመተግበር የምናደርገው ጥረት ነው።

Write comment (0 Comments)

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት