የቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ጥቅሶች

"ሰው በሕይወቱ እግዚአብሔር እንደሌለ ሆኖ ከኖረ፤ የእግዚአብሔርን ብቻ ሳይሆን የራሱንም ሆነ የዓለምን ምንነት ትርጉም ያጣል"

ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ "የሕይወት ብሥራት" በሚለው መልክታቸው ቁ.24

 

ቀጣይ ፈተና

"ፍቅር በቀጣይነት ከእግዚአብሔር ወደኛ የሚላክ ተፈታታኝ ጥያቄ ነው።" - (ከኛ መልስን በመሻት እግዚአብሔር አሁንም አሁንም እወድሃለሁ/እወድሻለሁ ይለናል)

 

ነጻነት ዒላማውን ሲስት

ነጻነት ዓላማ ከሌለው፣ በሰው ልጆች ልብ ውስጥ የተቀረጸውን ሕግ ለማወቅም ካልተመኘና የኅሊናንም ድምጽ መስማት ከተሳነው፣ ኅብረተሰብንና የሰው ልጅን ማጥፋት ይጀምራል። 

 

ባዶ ድኻ፤ ሙሉ ሀብታም የለም!

አንድ ሰው የመጨረሻ ድኻ ቢሆንም እንኳ ለሌላ ሊሰጥ የሚችለው ነገር አለው፤ እንዲሁም ሌላውም በጣም የተትረፈረፈው ሀብታም ቢሆንም ከሌላ ሰው መቀበል የሚያስፈልገው ነገር አለ።

 

የዓለም ዘግናኙ እስር ቤት - የራስ ልብ

ከእስር ቤቶች ሁሉ ዘግናኙ እስር ቤት በተዘጋ ልብ ውስጥ መኖር ነው።

 

የትንሣኤ ሕዝብ!

ራሳችሁን ለተስፋ ቁርጠት አሳልፋችሁ አትስጡ! እኛ የትንሣኤ ሕዝብ ነን፤ ዝማሬያችንም ሃሌሉያ ነው!

 

ነጻነት ኀላፊነት ነው

·በኃይልና ዓመፅ ለአንድ ኅብረተሰብ ፍትሕን ማምጣት አይቻልም፤ ዓመፅ ራሱ አመጣለሁ የሚለውን ፍትሕ ያጠፋዋል።

·ነጻነት ማለት የፈለግነውን ማድረግ የመቻል መብት ማለት ሳይሆን፤ ማድረግ የሚገባንን ማድረግ የመቻል መብት ነው።

·እውነተኛ ቅድስና ማለት ከዓለም መሸሽ ማለት አይደልም፤ ነገር ግን ወንጌልን በየአንዳንዷ የዕለታዊ ሕይወታችን ውስጥ በቤተሰብ፣ በትምህርት ቤት፣ በሥራ ቦታና በኅብረተሰብ ውስጥ ለመተግበር የምናደርገው ጥረት ነው።