የመጽሐፍ ቅዱስ መግቢያ - ትምህርት አንድ

Bible scrollበዚህ ክፍል ውስጥ በቀጣይነት የሚቀርቡት መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች ከእምድብር አገረ ስብከት ካህናት ሲሆን ዋና አዘጋጅ አባ ምሥራቅ ጥዩ፣ ምክትል አዘጋጅና አስተባባሪ ካህን ደግሞ አባ ፍቅረየሱስ ተስፋዬ ናቸው። ሐዋሪያዊ አገልግሎታቸውን እግዚአብሔር ይባርክ ዘንድ በጸሎታችን እንደግፋቸው እያልን ይህን ለዚህ ድረ ገጽ ስላበረከቱልን ደግሞ ምስጋናችን ብዙ ነው።የመጽሐፍ ቅዱስ መግቢያ - ትምህርት አንድ

► መጽሐፍ ቅዱስ ማለት ምን ማለት ነው? የቃሉስ አመጣጥ ከወዴትና ምንስ ያመለክታል? 

መጽሐፍ ቅዱስ ቃሉ እንደሚያመለክተው መጽሐፍ እና ቅዱስ የሚሉ የሁለት ቃላት ጥምረት ነው ፡፡ በግሪክ ቋንቋ ቢብሎስ (byblos) ከደንገል በተሠራ ወረቀት ወይም በብራና ከተጻፈ በኋላ በሁለት በትሮች የሚጠቀለል መጽሐፍ ያመለክታል ፡፡ ቢብሎስ በእንግሊዘኛው ባይብል ተብሎ ሲተረጎም በአማርኛው ደግሞ መጽሐፍ በሚለው ቃል ተተረጐመ ፡፡ የግሪኩ ቃል ቢብሎስ (byblos) እራሱ ቢብሎስ (byblos) ከተባለ ከተማ ስም የተገኘ ነው ፤ እርሱም ከኒቂያ ወደቦች መካከል በቤይሩት  25 ማይል ያህል ርቆ የሚገኝ አገር ነው ፡፡ ለመጽሐፍ ያገለግል ዘንድ ፓፒረስ (ደንገል) የተባለውን ተክል እንደ ወረቀት አድርገው ይሠሩበት የነበረ ቦታ ነው ፡፡ 

ሁለተኛው ተጠማሪ ቃል “ቅዱስ” የሚለው ሲሆን ትርጓሜውም የተለየ ማለት ነው ፡፡ ሰው ወይም ማንኛውም ነገር ለእግዚአብሔር አገልግሎት ሲለይ ቅዱስ ይባላል ፡፡ ሰዎች (ዘጸ 28, 41) ፣ እንስሳት (ዘጸ13, 2) ፣ ቦታዎች (ዘጸ 3, 5) ቀኖች (ዘፍ 2, 3) ፣ ማናቸውም ነገር ቅዱስ ሊባል ይችላል (ኢያሱ 6, 19) ፡፡  የመጽሐፍ ቅዱስ ጥምረት ወደሆነው “ቅዱስ” ወደሚለው ቃል ስንመጣ ደግሞ ይህ መጽሐፍ እንደማንኛውም ተራ መጽሐፍ የሚታይ ሳይሆን የተቀደሰና የተለየ መሆኑን ከማሳየቱም አልፎ የጻፉት ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተሞልተውና ተመርተው እንደነበር ያስገነዝባል ፡፡ በእርግጥም የጻፉት ሰዎች ከራሳቸው ልቦና ፈጥረው ወይም አንቅተው ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነትና በእግዚአብሔር እየተመሩና እየታዘዙ የጻፉት ነው (ዮሐ 14, 26) ፡፡ 

ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ህልውናውንና ፈቃዱን ረቂቅ ባሕሪውን በተወሰነ መልኩ የምንረዳበትንና ፈቃዱንም ምን እንደሆነ ማወቅ የምንችልበት በእግዚአብሔር በራሱ መንፈስ መሪነት የተጻፈና ለሰው ልጆች የተሰጠ(የተገለጸ) ቅዱስ ቃል ነው ፡፡ 

ቅዱስ ዮሐንስ እንደሚለው “ከመጀመሪያው ስለነበረው ስለ ሕይወት ቃል እንጽፍላችኋለን ፤ ይህ የሕይወት ቃል የሰማነውና በዐይኖቻችን ያየነው የተመለከትነውና በእጆቻችን የዳሰስነው ነው ፡፡ ይህ ሕይወት ተገልጦአል ፤ እኛም አይተነዋል ፤ እንመሰክራለንም ፡፡ በአብ ዘንድ የነበረውንና ለእኛም የተገለጠውን የዘላለም ሕይወት እንነግራችኋለን ፡፡ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተም እንነግራችኋለን ፡፡ ኅብረታችንም ከአብና ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው ፡፡ ደስታችንም ሙሉ እንዲሆን ይህን እንጽፍላችኋለን” (1 ዮሐ 1, 1-4) ፡፡ 

በአጠቃለይ መጽሐፍ ቅዱስ “ዘላለማዊ ሕግ” ሲሆን ዓላማውም ሰዎችን ለሰማያዊ መንግሥት ማብቃት ነው ፡፡ ስለዚህ ከሌሎች የሳይንስ ፣ የልቦለድና የፍልስፍና መጽሐፍት ፈጽሞ ይለያል ፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ መሪነት ከመጻፉ አልፎ የሚያነቡትና የሚሰሙትን የሚመክር ፣ የሚገስጽ ፣ የሚያረጋጋና ወደ ደኅንነት ሊያደርስ የሚችል ጥበብ ያለው በመሆኑ ነው (2 ጢሞ 3, 14-17 ፣ ሐዋ 13, 16) ፡፡ ከዚህም በላይ መጽሐፍ ቅዱስ ጣፋጭ የሆነ የሚበላ ሰማያዊ ስንቅ (ሕዝ 3, 1-3) ፣ ብርሃን ሆኖ የሚመራ (መዝ 119, ቁ. 105) ፣ አጽናኝና መካሪ መሆኑን በተለያዩ ቦታዎች ተገልጾ ይገኛል ፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ከእግዚአብሔር የተገኘና እርሱ በመረጣቸው ቅዱሳን ሰዎች በራሱ መንፈስ መሪነት የተጻፈና ከሰው ልጅም ጋር ቃል ኪዳን ያጸናበት ቅዱስ ቃል ነው ፡፡ 

በጥንት ዘመን ግን (እስከ 100 ዓ. ም ድረስ) የቅጠል ዓይነት መጽሐፍት (አሁን ያለው ዓይነት) ስላልነበር መጽሐፍ ቅዱስ የሚለው ቃል “ጥቅልል” በሚል ስም ይታወቅ ነበር ፡፡ የጥቅልል ርዝመት ዐሥር ሜትር ሊደርስ ይችል ነበር፡፡ ጽሕፈቱም በዐምዶች ላይ ነበር (ኢሳ 34, 4 ፣ ኤር 36, 2 እና 20-23 ፣ ሕዝ 3, 1-3 ፣ ሉቃ 4, 17-19 ፤ 2ዮሐ 12 ፣ ራእ 5, 1 ፣ 2ጢሞ 5, 13)፡፡ ባጠቃለይ መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈበት ዘመን በወረቀት ወይም በብራና የተጻፈውን ሲያመለክት የጥቅልል መጽሐፍ እንጂ በቅጠል ላይ የተጻፈ መጽሐፍ አልነበረም ፡፡

በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ የቅዱሳት መጻሕፍት መዝገብ ነው ፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን ናቸው ፡፡ ብሉይ ኪዳን ከ1400 - 400 ከክ.ል.በ በልዩ ልዩ ቦታዎች አርባ በሚያህሉ ልዩ ልዩ ጸሐፊዎች እንደተጻፈ ይነገራል ፡፡ አዲስ ኪዳን ከ45-96 ዓ. ም በስምንት ሰዎች ተጻፈ ፡፡ 

► መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር በራሱ መንፈስ መሪነት የተጻፈ ነው ተብሏል ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ሲጻፍ የእግዚአብሔር መንፈስ ለምን አስፈለገ ?

የእግዚአብሔር መንፈስ ካስፈለጉባቸው ጥቂት ምክንያቶች ውስጥ ለመጥቀስ ያህል ፦ 

► ቅዱሳት መጽሐፍት የጻፉት በምን ዓይነት መልኩ ነው ይህንን የእግዚአብሔር ቃል የተቀበሉት ? እንዴት ነው ይህ ቃል ወደ እነሱ ሊመጣና ሊጽፉት የቻሉት ? በምን ዐይነት መልክ ነው እግዚአብሔር ቃሉን ወደ እነሱ እንዲደርስ ያረገው?

እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ቃሉን ወደ ሚያደምጡት ቅዱሳኖች አስተላልፏል ፡፡ ቃሉ ለእነሱ ከመግለጹ በፊት ግን የእነሱ በጎ ፈቃደኝነት ይጠይቃል ፡፡ ማንም ሰው በእግዚአብሔር ተገዶና ነጻነቱ ተነፍጎ አይደለም የሚጽፈው ፡፡ ጸሐፊው በበጎ ፈቃደኝነቱና በነጻነት ራሱን ያዘጋጃል ፤ ከዚያም እግዚአብሔር የገለጸለትን ቃል በራሱ ቋንቋ ፣ ባሕልና የአጻጻፍ ዘይቤ መሠረት ቃሉን ይጽፋል ፡፡ እግዚአብሔርም ቃሉን በሚከተሉት መንገዶች ለጸሐፊዎች ይገልጻል ፦

► መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈበት ዋና ዓላማው ምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፉባቸው ዓለማዎች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ በጥቂቱ ለመግለጽ ያህል ፦

► መጽሐፍ ቅዱስ የብዙ መጻሕፍት መዝገብ ወይም ስብስብ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን እንዴት አድርጋ ነው እነዚህ መጻሕፍት ሁሉ አግኝታ በአንድ መጽሐፍ ውስጥ የሰበሰበቻቸው?

► የቅዱሳት መጻሕፍት ቀኖና ማለት ምን ማለት ነው? ቤ/ክ የቅዱሳት መጻሕፍት ብዛትና ይዘት ተቀብላ ከማጽደቋ ጋር ምን ግኑኝነት አለው ?

► ከመቼ ጀምሮ ነው መጽሐፍ ቅዱስ በምዕራፍና በቁጥር ተከፋፍሎ መነበብ የጀመረው ? 

► መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመርያ ጊዜ የተጻፈው በምን ቋንቋ ነው? አዲስ ኪዳንና ብሉይ ኪዳን በመባል የመከፈሉ ምክንያትስ ምንድን ነው? 

► መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ሀገራችን ቋንቋዎች (ግእዝና አማርኛ) መቼና በማን ተተረጎመ?

 

የትምህርቱ ዋና አዘጋጅ ፦ አባ ምሥራቅ ጥዩ

ምክትል አዘጋጅና አስተባባሪ ካህን ፦ አባ ፍቅረየሱስ ተስፋዬ

ጸሐፊ ፦ ሲስተር አበበች ጃቤ

ጥያቄዎች

  1. ከሚከተሉት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ ሲጻፍ የእግዚአብሔር መንፈስ ካስፈለጉባቸው ምክንያቶች ውስጥ የማይመደበው(የሌለው) የትኛው ነው? ሀ)ያለ ስህተትና ምንም ዐይነት ልዩነት ሳያንጸባርቅ እንዲጻፍ ለ)እግዚአብሔር የተናገረውን ተረድቶ ለመጻፍ ሐ) የእግዚአብሔር ቃል ምስጢራዊ ፣ ከሰው አእምሮና ጠቅላላ ችሎታ በላይ ስለሆነ መ) ሰው አመፀኛ ስለሆነ
  2. መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመርያ ጊዜ በምን ቋንቋ ተጻፈ? ሀ) ብሉይ ኪዳን በግሪክ አዲስ ኪዳን በአራማይስጥ ለ) ብሉይ ኪዳን በዕብራይስጥ አዲስ ኪዳን በአራማይስጥ ሐ) ብሉይ ኪዳን በዕብራይስጥ አዲስ ኪዳን በግሪክ መ) ብሉይ ኪዳ በግሪክ አዲስ ኪዳን በዕብራይስጥ
  3. ቤ/ክ የሃይማኖትን ትምህርት ለመግለጥና ለማስተማር በማለት የተለያዩ መስፈርቶች በመጠቀም ቅዱሳት መጽሐፍትን ይዘታቸው በደንብ አድርጋ አጥንታና መርምራ በጉባኤ (በሲኖዶስ) አቅርባ የምትወስንበት ሂደት ምን በመባል ይታወቃል ? 
  4. መጽሐፍ ቅዱስ ከሌሎች መጻሕፍት የሚለይበት ዋናው ምክንያት ምንድን ነው ?
  5. እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ቃሉን ወደ ሚያደምጡት ቅዱሳኖች አስተላልፏል ፡፡ ቅዱሳኖችም ይህንን ቃል በጽሑፍ አስፍረውታል ፡፡ እግዚአብሔር ቃሉን ወደ ሚያደምጡት ቅዱሳኖች መልእክቱን ለማስተላለፍ ከተጠቀመባቸው መንገዶች ውስጥ ሕልምና ራእይ ይገኙበታል ፡፡ ለመሆኑ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አኳያ ሕልምና ራእይ ልዩነታቸው ምንድን ነው ? 
  6. ሰዎች በዕለታዊ ሕይወታቸው ውስጥ አለመተማመን ሲጠፋ ወደ መማማል ይደርሳሉ ፤ በአንዳንድ ቦታዎች በተለይም በፍርድ ቤቶች ውስጥ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው ሲምሉ ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ሲያስምሉ ይታያል ፡፡ ለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ይዞ መማል ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ማስማል ምን ትርጉም አለው ? ለምንስ መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው ይምላሉ ?