እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የእንድርያስ ፡ ጥረት ፡ ከንቱ ፡ ልፋት ፡ ወይስ ፡ ብልህነት ?

የእንድርያስ ፡ ጥረት ፡ ከንቱ ፡ ልፋት ፡ ወይስ ፡ ብልህነት ?

በተመሳሳይ ፡ መልኩ ፡ የሐዋርያው ፡ እንድርያስ ፡ ጭንቀት ፡ ሌላው ፡ በወንጌላዊው ፡ ዮሐንስ ፡ ትኩረት ፡ የተሰጠው ፡ ትልቁ ፡ ነጥብ ፡ ነው ፡፡ በእርግጥም ፡ እንድርያስ ፡ ከሐዋርያቶች ፡ ሁሉ ፡ የመጀመርያ ፡ ሐዋርያ ፡ ብቻ ፡ ሳይሆን « መሲሁን ፡ አገኘነው ›› በማለት ፡ ትልቅ ፡ የምስክርነት ፡ ቃል ፡ ሰጥቶ ፡ የነበረ ፡ ነው ፡፡ በእብራይስጥ ፡ ቋንቋ « መሲሕ ›› ወይም ፡ በግሪክ ፡ ቋንቋ « ክርስቶስ ›› ማለት ፡ « የተቀባ ›› ማለት ፡ ነው ፡፡ ከብሉይ ፡ ኪዳን ፡ ዘመን ፡ « መቀባት ›› ለአገልገሎት ፡ መለየትንና ፡ መመደብን ፡ ያመለክታል ፤ በተለይም ፡ ንጉስ (1 ሳሙ 16 ፡ 11, 1 ሳሙ 26 ፡ 11) ወይም ፡ ካህን (ዘጸ 40 ፡ 13, ዘሌ 4፡ 3) መሆንን ፡ ያመለክታል ፡፡ ሆኖም ፡ ሰዎች ፡ ይፈልጉትና ፡ ይጠብቁት ፡ የነበረው ፡ በተለመደው ፡ ሥርዐት ፡ የተቀባ ፡ ሰው ፡ ሳይሆን ፡ ከእግዚአብሔር ፡ የተቀባውን ፡ ብቸኛ ፡ መሲህ ፡ ነበር ፡፡ ታድያ ፡ እንድርያስ ፡ ይህንን ፡ አብጠርጥሮ ፡ የተረዳና ፡ ያወቀ ፡ የመጀመርያው ፡ ሐዋርያ ፡ ሆኖ ፡ እያለ ፡ ነው ፡ ዛሬ ፡ ፈተና ፡ ሲገጥመው ፡ ሁሉን ፡ ነገር ፡ ረስቶና ፡ በሰብአዊነቱ ፡ ተረቶ ፡ ጭንቀት ፡ ውስጥ ፡ የገባው ፡፡ ለዚህም ፡ ነው ፡ የኢየሱስና ፡ የፊልጶስ ፡ ውይይት ፡ ሰምቶ ፡ መፍትሄ ፡ ፍለጋ ፡ የጀመረው ፡፡ ለእሱ ፡ አጠገቡ ፡ ቆሞ ፡ ያለውን ፡ ለጥያቄ ፡ ሁሉ ፡ መልስ ፡ ሊሰጥ ፡ የሚችለውን ፡ ኢየሱስን ፡ በመተውና ፡ ወደ ፡ ሕዝቡ ፡ ዘንድ ፡ በመሄድ ፡ እንጀራና ፡ ዓሣ ፡ መፈለግ ፡ ጀመረ ፡፡ በመጨረሻም ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ ፡ በመምጣት « አምስት ፡ ትንንሽ ፡ የገብስ ፡ እንጀራና ፡ ሁለት ፡ ትንንሽ ፡ ዓሣ ፡ የያዘ ፡ አንድ ፡ ልጅ ፡ እዚህ ፡ አለ ፤ ይህ ፡ ግን ፡ ለዚህ ፡ ሁሉ ፡ ሕዝብ ፡ እንዴት ፡ ይዳረሳል ?›› በማለት ፡ ጭንቀቱን ፡ ሲገልጽ ፡ ይታያል ፡፡

እዚህ ፡ ላይ ፡ እንድርያስ ፡ በአንድ ፡ መልኩ ፡ ሁሉን ፡ ቻይና ፡ ሁሉን ፡ አድራጊ ፡ የመፍትሄዎች ፡ ሁሉ ፡ ቁልፍ ፡ የሆነውን ፡ ኢየሱስን ፡ ረስቶ ፡ ለመፍትሄ ፡ ወደ ፡ ሌላ ፡ ቦታ ፡ መሯሯጡ ፡ ድክመቱን ፡ ቢያሳይም ፡ በሌላ ፡ መልኩ ፡ ግን ፡ ያገኛትን ፡ ትንሿንም ፡ ነገር ፡ ቢሆን ፡ ይዞ ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ ፡ በመምጣት ፡ « ለዚህ ፡ ሁሉ ፡ ሕዝብ ፡ እንዴት ፡ ይደርሳል ?›› በማለት ፡ መጠየቁን ፡ ከፊሊጶስ ፡ በላይ ፡ የእሱ ፡ እምነት ፡ የጠነከረና ፡ አስተዋይነቱም ፡ የላቀ ፡ መሆኑን ፡ ያሳያል ፡፡ ምክንያቱም ፡ ያለውን ፡ ትንሿንም ፡ ነገር ፡ ይዞ ፡ በመቅረብ ፡ ለኢየሱስ ፡ ጥያቄ ፡ ማቅረቡን « ያገኘሁትን ፡ ትንሽ ፡ ነገር ፡ ነው ፤ አንተ ፡ እንደሚሆን ፡ አድርገው ›› ብሎ ፡ በሱ ፡ ላይ ፡ መተማመኑን ፡ ያሳያል ፡፡ አንዳንድ ፡ ሊቃውንቶች ፡ ሲያክሉም ፡ እንድርያስ ፡ ባዶ ፡ እጁ ፡ ሳይሆን ፡ የሆነ ፡ ነገር ፡ ይዞ ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ ፡ ቀርቦ ፡ መፍትሄ ፡ እንዲሰጠው ፡ መጠየቁ ፡ ብልህነቱን ፡ ይገልጻል ፤ ምክንያቱም ፡ የራሱ ፡ የሆነ ፡ ሰብአዊ ፡ ጥረት ፡ ካደረገ ፡ በኋላ ፡ ነው ፡ ያገኛውን ፡ ነገር ፡ ትንሽ ፡ ነው ፡ ሳይል ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ ፡ የተጓዘው ፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት