እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የወንጌሉ ፡ መልእክት ፡ ማን ፡ ላይ ፡ ያተኩራል

የወንጌሉ ፡ መልእክት ፡ ማን ፡ ላይ ፡ ያተኩራል

በዮሐ 6 ፡ 1-15 የተካተቱት ፡ ዋና ፡ ዋና ፡ ገጸ ፡ ባሕርያት ፡ ሦስት ፡ ሲሆኑ ፡ ሌላ ፡ ተጨማሪ ፡ የሆነ ፡ አራተኛ ፡ ገጸ ፡ ባሕርይም ፡ ይገኛል ፡፡ እነዚህም ፡ ኢየሱስ ፣ ሐዋርያቶች ፣ ሕዝቡ ፡ እና ፡ እንጀራና ፡ ዓሣ ፡ የያዘ ፡ አንድ ፡ ትንሽ ፡ ልጅ ፡ ናቸው ፡፡ በተለምዶ ፡ ሕዝቡ ፡ ኢየሱስ ፡ ወደሚገኝበት ፡ ስፍራ ፡ ይሄድ ፡ የነበረው ፡ በሽተኞችን ፡ በመያዝ ፡ ፈውስ ፡ ለማግኘትና ፡ ትምህርቱን ፡ ለማድመጥ ፡ ነበር ፤ በዚህ ፡ ታሪክ ፡ ውስጥ ፡ ግን ፡ ሕዝቡ ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ ፡ ለመሄድ ፡ ያነሳሳው ፡ የራሱ ፡ የሆነ ፡ ውስጣዊ ፡ ፍላጎት (ልባዊ ፡ መሻት) ፡ ነው ፡፡ በዚህም ፡ ውስጣዊ ፡ ፍላጎት ፡ ተገፋፍቶ ፡ ነው ፡ የኢየሱስን ፡ ትምህርት ፡ ለማድመጥ ፡ ቀዬውን ፡ ጥሎ ፡ ራቅ ፡ ወዳለ ፡ ቦታ ፡ እንደሄደ ፡ የተገለጸው ፡፡ እንግዲህ ፡ ኢየሱስ ፡ ያስተምራል ፡ ሕዝቡ ፡ ደግሞ ፡ መንፈስንና ፡ ሥጋን ፡ የሚያረካውን ፡ አጥንትና ፡ ጅማትን ፡ የሚቆራርጠውን ፡ ቃሉን ፡ እያደመጠና ፡ መንፈሱን ፡ እየመገበ ፡ ቆይታውን ፡ አስረዝሟል ፡፡ በጌ.ኢ.ክ ፡ ፊት ፡ ተገኝቶ ፡ ቃሉን ፡ መስማትና ፡ ነፍስን ፡ ማደስ ፡ ሁሉንም ፡ ነገር ፡ ያስረሳል ፡ ከሁሉም ፡ ነገር ፡ ይበልጣልና ፡ ጊዜው ፡ ሳይታወቅ ፡ እጅግ ፡ በጣም ፡ ሄደ ፡፡ ኢየሱስ ፡ ስለምን ፡ እንዳስተማራቸው ፡ ግን ፡ ምንም ፡ አልተገለጸም ፡፡ እዚያ ፡ ቦታ ፡ ላይ ፡ ግን ፡ ለረጅም ፡ ጊዜ ፡ አብረው ፡ እንደቆዩ ፡ ተገልጿል ፡፡ ቀጥሎም ፡ የሕዝቡን ፡ ረሃብ (የምግብ ፡ ጥያቄ) ታሪኩ ፡ እንደቀየረውና ፡ ውይይቱም ፡ ወደ ፡ ጌ.ኢ.ክ ፡ እና ፡ ወደ ፡ ሐዋርያቶች ፡ እንደዞረ ፡ እናያለን ፡፡ በአጠቃላይ ፡ የወንጌሉ ፡ ተኩረት ፡ በጌ.ኢ.ክ ፡ በሕዝቡና ፡ በሕዝቡ ፡ ረሃብ ፡ ላይ ፡ መሆኑን ፡ በደንብ ፡ ይንጸባረቃል ፡፡ ታድያ ፡ ረሃቡ ፡ ምንን ፡ ያመለክታል ፡፡ የሥጋ ፡ ወይስ ፡ የመንፈስ ፡ ረሃብ ፡ ነበር ? ረሃቡ ፡ ለማስታገስስ ፡ ታምራት ፡ ማከናወን ፡ ያስፈልግ ፡ ነበርን ? ተሰብስበው ፡ የሚገኙበትስ ፡ ቦታ (ተራራ ፡ ላይ) ፡ ከረሃቡና ፡ ከጥማቱ ፡ ጋር ፡ በተያያዘ ፡ መልኩ ፡ ለየት ፡ ያለና ፡ ማስተላለፍ ፡ የፈለገው ፡ መልእክት ፡ ይኖር ፡ ይሆን ?

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት