እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ ለምን ፡ አይቆጠሩም

ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ ለምን ፡ አይቆጠሩም

ይህንን ፡ የአምስት ፡ እንጀራና ፡ የሁለት ፡ ዓሣ ፡ ታሪክ ፡ በምናነብበት ፡ ጊዜ ፡ ሌላው ፡ ሳናስተውለው ፡ ማለፍ ፡ የሌለብን ፡ ጉዳይ ፡ ቢኖር ፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ አለመጠቀሳቸው ፡ ወይም ፡ ጭራሽ ፡ ቁጥር ፡ ውስጥ ፡ አለመግባታቸው ፡ ነው ፡፡ ቅ.ማርቆስ ፣ ሉቃስ ፡ እና ፡ ዮሐንስ ፡ ጭራሽ ፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ በቦታው ፡ እንደነበሩም ፡ አይጠቀሱም ፡፡ እንዲያው ፡ በደፈናው ፡ እንጀራውንና ፡ ዓሣውን ፡ የበሉት ፡ አምስት ፡ ሺህ ፡ ወንዶች ፡ ነበሩ ፡ በማለት ፡ ያልፉታል (ማር 6 ፡ 44 ሉቃ 9 ፡ 14 ዮሐ 6፡ 10) ፡፡ ቅ. ማቴዎስ ፡ ግን « የበሉትም ፡ ከሴቶችና ፡ ከሕፃናት ፡ ሌላ ፡ አምስት ፡ ሺህ ፡ ወንዶች ፡ ያህል ፡ ነበሩ ›› (ማቴ 14 ፡ 21) በማለት ፡ እዚያ ፡ ቦታ ፡ ላይ ፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ እንደነበሩ ፡ ነገር ፡ ግን ፡ ከበላተኛው ፡ ጋር ፡ እንዳልተቆጠሩ ፡ አበክሮ ፡ ይገልጻል ፡፡ በወቅቱ ፡ ሴቶች ፡ የኢየሱስ ፡ ትምህርት ፡ ለመስማት ፡ አይሄዱም ፡ ነበር ፡ እንዳንል ፡ እጅግ ፡ በጣም ፡ ጎበዝ ፡ የሆኑና ፡ እስከ ፡ መስቀል ፡ ሥር ፡ የተከተሉት ፡ በኋላም ፡ ትንሣኤውን ፡ ለመጀመርያ ፡ ጊዜ ፡ ያወጁት ፡ ሴቶች ፡ እንደነበሩ ፡ በወንጌል ፡ ውስጥ ፡ ተበክሮ ፡ ተገልጿል ፡፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ ስላልበሉ ፡ አልተቆጠሩም ፡ እንዳይባል ፡ ከማንኛውም ፡ የዕድሜ ፡ ክልል ፡ ውስጥ ፡ ካሉት ፡ ሰዎች ፡ መካከል ፡ ሲርባቸው ፡ ምግብ ፡ ይሰጠን ፡ በማለት ፡ በማልቀስም ፡ ሆነ ፡ በተለያየ ፡ ጉትጎታ ፡ እረፍት ፡ የሚነሱት ፡ ሕፃናቶች ፡ እንደሆኑ ፡ የታወቅ ፡ ነው ፡፡ ስለዚህ ፡ ጎረምሶች ፡ እየበሉ ፡ ሕፃናት ፡ ዝም ፡ ብለው ፡ ረሃባቸው ፡ ዋጥ ፡ አርገው ፡ ቆመው ፡ ይመለከቱ ፡ ነበር ፡ ለማለት ፡ በጣም ፡ ያስቸግራል ፡፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ (ወደ ፡ አንድ ፡ መምህር) ፡ ለመቅረብ ፡ አይደፍሩም ፡ ወይም ፡ ባሕሉ ፡ አይፈቅድላቸውም ፡ ነበር ፡ እንዳንል ፡ ኢየሱስ ፡ እራሱ « ሕፃናት ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ እንዲመጡ ፡ ፍቀዱላቸው ፤ አትከልክሏቸው ፡ የእግዚአብሔር ፡ መንግሥት ፡ እንደነዚህ ፡ ላሉት ፡ ነውና ›› (ሉቃ 18 ፡ 16) ፡ ብሎ ፡ እራሱ ፡ ተናግሯል ፡፡ ታድያ ፡ ወንጌላውያን ፡ ትኩረታቸው ፡ ለምን ፡ ወንዶቹ ፡ ላይ ፡ ብቻ ፡ ሆነ ? ለምን ፡ ሴቶችንና ፡ ሕፃናት ፡ ከቁጥር ፡ ውጪ ፡ ማድረጉን ፡ ፈለጉት ?

በዚህ ፡ ዙርያ ፡ የኢትዮጵያ ፡ አንድምታ ፡ እንዴት ፡ እንደሚተነትነው ፡ ቃኘት ፡ አርገን ፡ የበለጠ ፡ አሳማኝ ፡ የሆነ ፡ ትንታኔ ፡ ወይም ፡ ትርጓሜ ፡ ወደተባለው ፡ ሀሳብ ፡ እንመለሳለን ፡፡ አንድምታ ፡ ማለት ፡ ኢተዮጵያውያን ፡ የቤተክርስትያን ፡ ሊቃውንት ፡ ከጥንት ፡ ጀምረው ፡ መጽሐፍ ፡ ቅዱስንና ፡ ሌሎችም ፡ የሊጡርጊያ ፡ መጽሐፍት ፡ በሕላችን ፣ ቋንቋችን ፣ የክርስትና ፡ ሐይማኖታች ፣ ታሪካችንና ፡ ባጠቃላይ ፡ የአገራችንን ፡ ማህበራዊ ፡ ሕይወት ፡ ግንዛቤ ፡ ውስጥ ፡ በማስገባት ፡ የእግዚአብሔርን ፡ ቃል ፡ ሕዝባችን ፡ የበለጠ ፡ ሊረዳው ፡ በሚችለው ፡ መልኩ ፡ የሚሰጡት ፡ ትንታኔ ፡ ወይም ፡ የትንታኔ ፡ ዘይቤ ፡ ነው ፡፡ አንድምታ ፡ ማቴ 14 ፡ ላይ ፡ የሕፃናትና ፡ የሴቶች ፡ አለመቆጠር ፡ ሁለት ፡ ምክንያቶች ፡ ይሰጣል ፡፡ እንደ ፡ አንድምታ ፡ አገላለጽ ፡ ሴቶች ፡ ሰው ፡ በተሰበሰበበት ፡ ቦታ ፡ ላይ ፡ ስለሚያፍሩ ፡ ብዙም ፡ አይበሉም ፡ ስለዚህ ፡ በደንብ ፡ ካልበሉ ፡ ደግሞ ፡ እንደበላ ፡ ሰው ፡ አይቆጠሩም ፡፡ ሕፃናት ፡ ደግሞ ፡ ከሚበሉት ፡ ይልቅ ፡ የሚያበላሹት ፡ ይበልጣልና ፡ እንደ ፡ በላተኛ ፡ ሊቆጠሩ ፡ አይገባም ፡ በማለት ፡ አንድምታ ፡ ሴቶችንና ፡ ሕፃናትን ፡ ያልተቆጠሩበት ፡ ምክንያት ፡ ይተነትናል ፡፡ ከዚህም ፡ በተጨማሪ ፡ እንደ ፡ አንድምታ ፡ አገላለጽ ፡ « የተረፈውንም ፡ ከመግደላዊት ፡ ማርያም ፡ ቤት ፡ አኑረውት ፡ በዘመነ ፡ ደዌ ፡ ለፈውስ ፡ በዘመነ ፡ ቀጠና ፡ ለበረከት ፡ ይወስዱት ፡ ነበር ›› ይላል ፡፡

በእርግጥ ፡ አንድምታ ፡ የሚያብራራው ፡ የአገራችንን ፡ ባሕላዊ ፡ አኗኗር ፡ በተለይም ፡ አንድምታ ፡ በተጻፈበት ፡ በአሥራ ፡ ሰባተኛውና ፡ በአሥራ ፡ ስምንተኛው ፡ ክፍለ ፡ ዘመን ፡ የነበረውን ፡ የአኗኗር ፡ ዘይቤ ፡ በመመርኮዝ ፡ ነው ፡፡ ሁላችንም ፡ እንደምንረዳው ፡ በተለይም ፡ በገጠሩ ፡ የአገራችን ፡ ክፍል ፡ የሚገኙ ፡ ሴቶች ፡ እንኳንስ ፡ በሺህ ፡ የሚቆጠር ፡ ሕዝብ ፡ በተሰበሰበበት ፡ ቦታ ፡ ይቅርና ፡ እቤት ፡ ውስጥ ፡ እንኳን ፡ አንድ ፡ እንግዳ ፡ ቢገኝ ፡ ወይም ፡ እንግዳ ፡ ሆነው ፡ ወደ ፡ አንድ ፡ ቤተሰብ ፡ ዘንድ ፡ ቢሄዱም ፡ ብዙ ፡ ከመብላት ፡ ይቆጠባሉ ፡፡ ሰው ፡ ሳያያቸው ፡ ዞር ፡ ብለው ፡ ብዙ ፡ ይበላሉ ፡ ማለት ፡ ሳይሆን ፡ በተፈጥሮ ፡ የማፈርና ፡ በባሕልም ፡ ውስጥ ፡ የአኗኗር ፡ ዘይቤአቸው ፡ እንደዚያ ፡ አይነት ፡ የማፈርና ፡ በይሉኝታ ፡ የመኖር ፡ ጫና ፡ ስለሚፈጥርባቸው ፡ ነው ፡፡  ወንጌሉ ፡ በተጻፈበት ፡ ጊዜ ፡ ከነበረው ፡ የሕዝቡ ፡ ማሕበራዊና ፡ ታሪካዊ ፡ አኗኗር ፡ ጋር ፡ ሲታይ ፡ ግን ፡ ሌላ ፡ ተጨማሪ ፡ ማብራሪያ ፡ እንዳለው ፡ ይገለጻል ፡፡

ይህም ፡ በወቅቱ ፡ ገሊላም ፡ ሆነ ፡ ኢየሩሳሌም ፡ ይገኙ ፡ የነበረው ፡ በሮማውያን ፡ ቅኝ ፡ ግዛት ፡ ሥር ፡ ነበር ፡፡ በዚህም ፡ ምክንያት ፡ ገዢዎቹ ፡ ሮማውያን ፡ ባሕላቸውን ፡ በአይሁዳውያን ፡ ሕዝብ ፡ ዘንድ ፡ በውዴታም ፡ ሆነ ፡ በግዴታ ፡ በደንብ ፡ አስፋፍተውት ፡ እንደነበር ፡ ይታወቃል ፡፡ ወንጌላውያንም ፡ አድማጮቻቸውን ፡ ወይም ፡ ያስተምሩት ፡ የነበረውን ፡ ማህበረሰብ ፡ በሮማውያን ፡ ያኗኗር ፡ ሁኔታ (ባሕል) ፡ ውስጥ ፡ ሰርጾ ፡ ገብቶ ፡ ስለነበር ፡ በሚጽፉትም ፡ ወንጌል ፡ ውስጥ ፡ የሮማውያንን ፡ ያኗኗር ፡ ዘይቤ ፡ ያንጸባርቁ ፡ እንደነበር ፡ ይታወቃል ፡፡ በጊዜው ፡ በነበሩት ፡ ሮማውያን ፡ የኑሮ ፡ ሂደት ፡ ውስጥ ፡ ደግሞ ፡ አንድ ፡ ግበዣ ፡ ካለ ፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ የራሳቸው ፡ የሆነ ፡ የተለየ ፡ ቦታ ፡ ላይ ፡ ሆነው ፡ ይመገቡ ፡ እንደነበረና ፡ ወደ ፡ ዋናው ፡ የግብዣ ፡ ቦታ ፡ ገብተው ፡ መመገብ ፡ ለእነሱ ፡ የተከለከለ ፡ እንደነበር ፡ ይገለፃል ፡፡ ለምሳሌ ፡ ሄሮድስ ፡ በተወለደበት ፡ ዕለት ፡ ለከፍተኛ ፡ ሹማምንቱ ፣ ለጦር ፡ አዛዦቹንና ፡ በገሊላ ፡ ለታወቁ ፡ ታላላቅ ፡ ሰዎች ፡ ገብዣ ፡ አደረገ ፡፡ የሄሮድያዳም ፡ ልጅ ፡ ገብታ ፡ በዘፈነች ፡ ጊዜ ፡ ሄሮድስንና ፡ ተጋባዦቹን ፡ ደስ ፡ አሰኘቻቸው ፡፡ ንጉሡም ፡ ብላቴናዪቱን ፡ የምትፈልጊውን ፡ ሁሉ ፡ ጠይቂኝ ፡ እሰጥሻለሁ ፡ ሲላት ፡ እሷም ፡ ወጥታ ፡ እናቷን ፡ ምን ፡ ልለምነው ፡ ብላ ፡ እንደጠየቀቻት ፡ ተገልጿል (ማር 6 ፡ 21-24) ፡፡ እዚህ ፡ ላይ ፡ ሁለት ፡ ነገሮች ፡ ማስተዋል ፡ ይኖርብናል ፡፡ በመጀመርያ ፡ የሄሮድያዳ ፡ ልጅ ፡ ለመዝፈንና ፡ እንግዶቹን ፡ ለማስደሰት ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ከውጪ ፡ ወደ ፡ ግብዣው ፡ አዳራሽ ፡ የገባችው ፡፡ ቀጥሎም ፡ እናትዬው ፡ ያለችው ፡ ከግብዣው ፡ አዳራሽ ፡ ውጪ ፡ መሆኑን ፡ ተጠቅሷል ፤ በእርግጥም ፡ ልጅትዋ ፡ እናትዋ ፡ ወደነበረችበት ፡ ከግብዣው ፡ አዳራሽ ፡ ውጪ ፡ ወደነበረው ፡ ለየት ፡ ወዳለው ፡ ቦታ ፡ ወጥታ ፡ በመሄድ ፡ ነው ፡ የጠየቀቻት ፡፡

በአጠቃላይ ፡ የሴቶችና ፡ የሕፃናት ፡ በወንጌሉ ፡ ውስጥ ፡ አለመቆጠራቸው ፡ ከዚህ ፡ የሮማውያን ፡ ባሕል ፡ ጋር ፡ በተያያዘ ፡ መልኩ ፡ ሲብራራ ፡ መልእክቱ ፡ የበለጠ ፡ ትርጉም ፡ እንደሚሰጥ ፡ ይገለጻል ፡፡ ይህም ፡ ማለት ፡ በወቅቱ ፡ ከነበረው ፡ ታሪካዊና ፡ ባሕላዊ ፡ የአኗኗር ፡ ዘይቤ ፡ አኳያ ፡ ሲታይ ፡ ሴቶችና ፡ ሕፃናት ፡ በግብዣ ፡ ቦታ ፡ ላይ ፡ የራሳቸው ፡ የሆነ ፡ የተለየ ፡ ቦታ ፡ ላይ ፡ ይገኙ ፡ ስለነበርና ፡ ወንጌላውያኑ ፡ ደግሞ ፡ የወቅቱ ፡ ባሕል ፡ በጠበቅ ፡ መልኩ ፡ ያስተምሩ ፡ ስለነበር ፡ ምንም ፡ እንኳ ፡ ሕዝቦቹ ፡ ሁሉ ፡ በኢየሱስ ፡ ዙርያ ፡ ሁሉም ፡ በአንድነት ፡ ቢገኙም ፡ ለወንጌላውያኑ ፡ የቁጥሩ ፡ አስፈላጊነት ፡ ለሚያስተምሩት ፡ ማሕበረሰብ ፡ ትርጉም ፡ ሰጪነቱ ፡ እስከዚህም ፡ ስለነበር ፡ ትኩረት ፡ አልሰጡትም ፡ ይሆናል ፡፡ በሌላ ፡ መልኩ ፡ ደግሞ ፡ አምስት ፡ ሺህ ፡ የሚያህሉ ፡ ወንዶች ፡ በልተው ፡ ነው ፡ ከአምስት ፡ እንጀራና ፡ ሁለት ፡ ዓሣ ፡ ላይ ፡ አሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ ትርፍራፊ ፡ የተሰበሰበው ፡ ብለው ፡ ወንጌላውያኑ ፡ ቢገልጹ ፡ ነው ፡ አንባቢያቸው ፡ ወይም ፡ አድማጫቸው ፡ በኢየሱስ ፡ ሥራ ፡ የበለጠ ፡ ሊገረም ፡ የሚችለው ፡፡ ከልሆነ ፡ አንባቢው ፡ አሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ የተረፈ ፡ ምግብ ፡ ተሰበሰበ ፡ የሚለው ፡ ሲያይ ፡ ይሄኔ ፡ እኮ ፡ ሕፃናት ፡ እና ፡ ሴቶች ፡ ብቻ ፡ በልተው ፡ ነው ፡ ያን ፡ ያህል ፡ ሊተርፍ ፡ የቻለው ፡ ብሎ ፡ ታምራቱን ፡ አቅልሎ ፡ እንዳያየውም ፡ ጭምር ፡ ሊሆን ፡ ይችላል ፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት