እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በአምስት ፡ ትንንሽ ፡ የገብስ ፡ እንጀራና ፡ በሁለት ፡ ትንንሽ ፡ ዓሣ ፡ ከአምስት ፡ ሺህ ፡ ሰው ፡ በላይ ፡ መመገብ ፡ እውነተኛ ፡ ታምር ፡ ወይስ ፡ አጠራጣሪ ፡ አስማት ?

በአምስት ፡ ትንንሽ ፡ የገብስ ፡ እንጀራና ፡ በሁለት ፡ ትንንሽ ፡ ዓሣ ፡ ከአምስት ፡ ሺህ ፡ ሰው ፡ በላይ ፡ መመገብ ፡ እውነተኛ ፡ ታምር ፡ ወይስ ፡ አጠራጣሪ ፡ አስማት ? (ዮሐ 6, 1-15)

መግቢያ

በመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ውስጥ ፡ ተካተው ፡ ከሚገኙትና ፡ በጌ.ኢ.ክ ፡ ከተከናወኑት ፡ ድንቅ ፡ ድንቅ ፡ ታምራቶች ፡ ውስጥ ፡ አንዱ ፡ ጌ.ኢ.ክ ፡  ከአምስት ፡ ሺህ ፡ ሰዎች ፡ በላይ ፡ በአምስት   ፡ ትንንሽ ፡ የገብስ ፡ እንጀራና ፡ በሁለት ፡ ትንንሽ ፡ ዓሣ ፡ መመገቡና ፡ ዐሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ የተረፈ ፡ ምግብ ፡ መሰብሰቡ ፡ ነው ፡፡ ይህንን ፡ ታሪክ ፡ የሚተርከው ፡ የወንጌል ፡ ክፍል ፡ ደግሞ ፡ በአራቱም ፡ ወንጌላውያን ፡ ተብራርቶና ፡ እንደውም ፡ ተደጋግሞ ፡ ተገልጾአል (ማር 6 ፡ 30-44 ማቴ 14 ፡ 13-21 ሉቃ 9 ፡ 10-17 ዮሐ 6 ፡ 1-15) ፡፡ ከዚህም ፡ በላይ ፡ አንዳንድ ፡ ወንጌላውያን ፡ ለዚህ ፡ የወንጌል ፡ ክፍል ፡ ልዩ ፡ ትኩረት ፡ ከመስጠታቸው ፡ የተነሳ ፡ ደጋግመው ፡ ጽፈውታል(ማር 6 ፡ 30-44 ማር 8 ፡ 2-9) ፡፡ ምንም ፡ እንኳን ፡ አራቱም ፡ ወንጌላውያን ፡ ይህንን ፡ የወንጌል ፡ ክፍል ፡ ከሞላ ፡ ጎደል ፡ በተመሳሳይ ፡ መልኩ ፡ ቢተርኩትም ፡ ወንጌላዊው ፡ ዮሐንስ ፡ ግን ፡ የበለጠ ፡ ትኩረት ፡ በመስጠት ፡ ለሚያስተምረው ፡ የክርስቲያን ፡ ማሕበረሰብ ፡ ጥልቅ ፡ የሆነ ፡ መልእክት ፡ ያስተላልፋል ፡ ባለ  ፡ መልኩ ፡ አንዳንድ ፡ ተጨማሪ ፡ ነገሮች ፡ በማካተት ፡ ሰፋ ፡ አድርጎ ፡ ተርኮታል ፡፡ በእርግጥም ፡ ወንጌላዊው ፡ ቅዱስ ፡ ዮሐንስ ፡ የጌታን ፡ እራት ፡ ወይም ፡ የቅዱስ ፡ ቁርባን ፡ አመሰራረት ፡ የሚገልጸውና ፡ በሌሎች ፡ ወንጌላውያን ፡ በደንብ ፡ ተብራርቶና ፡ በሰፊው ፡ ተተንትኖ ፡ የቀረበው ፡ የወንጌል ፡ ክፍል ፡ አልጻፈውም ፡፡ በዚህ ፡ ምትክ ፡ ግን ፡ ከሌሎች ፡ ወንጌላውያን ፡ በተለየ ፡ መልኩ ፡ ጌ.ኢ.ክ ፡ የሓዋርያቶችን ፡ እግረ ፡ በማጠብ ፡ ትህትናን ፡ ያስተማረበትንና ፡ ሌሎች ፡ ከጌታ ፡ እራት ፡ ጋር ፡ ተዛማጅነት ፡ ያላቸው ፡ ታምራትንና ፡ ታሪኮችን ፡ በጥልቀት ፡ አብራርቶ ፡ ጽፎአል ፡፡ ከእነዚህም ፡ ውስጥ ፡ አንዱ ፡ የሆነውና ፡ ከጌታ ፡ እራት ፡ ጋር ፡ በተዛማጅነት ፡ የተጻፈው ፡ ከላይ ፡ በመግቢያው ፡ የተጠቀሰው ፡ ጌ.ኢ.ክ ፡ በአምስት ፡ ትንንሽ ፡ የገብስ ፡ እንጀራና ፡ በሁለት ፡ ትንንሽ ፡ ዓሣ ፡ ከአምስት ፡ ሺህ ፡ በላይ ፡ የሆኑ ፡ ሰዎችን ፡ መመገቡን ፡ የሚገልጸው ፡ የወንጌል ፡ ክፍል ፡ ነው ፡፡

ስለዚህ ፡ ምንም ፡ እንኳን ፡ በዚህ ፡ ታሪክ ፡ ዙርያ ፡ በአራቱም ፡ ወንጌላውያን ፡ የተብራሩት ፡ ነገሮች ፡ ግንዛቤ ፡ ውስጥ ፡ ብናስገባም ፡  ለዚህ ፡ አጭር ፡ የሆነው ፡ የወንጌል ፡ ጥናት ፡ የምናተኩረው ፡ ግን ፡ በወንጌላዊው ፡ ቅዱስ ፡ ዮሐንስ ፡ የተገለጸው ፡ የወንጌል ፡ ክፍል (ዮሐ 6  ፡ 1-15) ፡ ይሆናል ፡፡ ታድያ ፡ ይህንን ፡ የወንጌል ፡ ክፍል ፡ በመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ሊቃውንት ፡ ዘንድ ፡ በስፋትና ፡ በጥልቀት ፡ ከተብራራ ፡ በኃላ ፡ አንዳንድ ፡ ጥያቄዎች ፡ ማስነሳቱ ፡ አልቀረም ፡፡ ይህም ፡ እንጀራና ፡ ዓሣ ፡ አባዝቶ ፡ ማደል ፡ ከዚያም ፡ ዐሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ የሚያህል ፡ ትርፍራፊ ፡ መሰብሰብ ፡ እንደ ፡ ታምር ፡ መታየት ፡ አለበት ፡ ወይስ ፡ እንደ ፡ አስማት (ምትሓት) ? እንጀራና ፡ ዓሣ ፡ ቁስአካላዊ ፡ ነገሮቸ ፡ ከመሆናቸው ፡ የተነሳ ፡ ለማባዛት ፡ የሚከብድ ፡ ቢሆንም ፡ ይህንን ፡ ሁሉን ፡ ቻይ ፡ በሆነው ፡ በጌ.ኢ.ክ ፡ እጅ ፡ በመከናወኑ ፡ ላይደንቀን ፡ ይችላል ፤ ነገር ፡ ግን ፡ ከዚህ ፡ ጋር ፡ በተያያዘ ፡ መልኩ ፡ አንዳንድ ፡ ጥያቄዎች ፡ ማስነሳቱ ፡ ግን ፡ አልቀረም ፡፡

ከእነዚህም ፡ ጥያቄዎቸ ፡ መካከል ፡ ጥቂቶቹን ፡ ብናይ ፡ ጌ.ኢ.ክ ፡ ሕሙማን ፡ ቢፈውስ ፡ በሥጋና ፡ በመንፈስ ፡ በሽታ ፡ የሚሰቃዩትን ፡ ለማዳን ፡ ነው ፡፡ ሙታንን ፡ ቢያስነሳ ፡ ሕይወትን ፡ በድጋሚ ፡ እንዲያገኙና ፡ የእግዚአብሔርን ፡ ድንቅ ፡ ሥራ ፡ እንዲያዩ ፡ ነው ፡ ከተባለ ፡ እንጀራና ፡ ዓሣስ ፡ አባዝቶ ፡ ማከፋፈል ፡ ለምን ፡ አላማ ፡ ተደረገ ፡ ሊባል ፡ ነው ?  ምንአልባትም ፡ ረሃብን ፡ ለማስታገስና ፡ ከረሃብ ፡ ጋር ፡ ተያይዞ ፡ ሊመጣ ፡ የሚችለዉን ፡ ድካም ፡ ለማራቅ ፡ ነው ፡ ሊባል ፡ ይችል ፡ ይሆናል ፤ ነገር ፡ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደዚህ ፡ አይነት ፡ ድንቅ ፡ ነገሮች ፡ እነዲከናወኑ ፡ የሚፈቅድ ፡ ከሆነ ፡ ታዲያ ፡ ዛሬስ ፡ በዓለማችን ፡ በተለያዩ ፡ ቦታዎች ፡ የሚበሉትና ፡ የሚጠጡት ፡ አጥተው ፡ በረሃብና ፡ በጥማት ፡ ለሚሰቃዩትን ፡ ልጆቹ ፡ ለምን ፡ እንደ ፡ ጥንቱ ፡ መና ፡ አያዘንብላቸውም ?  በተጨማሪም ፡ ሙሴና ፡ አሮን ፡ ወደ ፡ ፈርዖን ፡ ዘንድ ፡ ሄደው ፡ የመጀመርያው ፡ ታምር ፡ ሲያደርጉ (በትርን ፡ ወደ ፡ እባብነት ፡ ሲቀይሩ) ፡ ፈርዖን ፡ ጠቢባኑና ፡ መተተኞቹን ፡ ጠርቶ ፡ በጥበባችው ፡ ያለ ፡ ምንም ፡ ችግርና ፡ ጭንቀት ፡ ተመሳሳይ ፡ ነገር ፡ እንዳከናወኑ ፡ ተገልጾ ፡ እናገኛለን (ዘፀ 7 ፡ 10-11) ፡፡ በግብጻውያን ፡ ዘንድ ፡ እንጂ ፡ በእስራኤላውያን ፡ የሕይወት ፡ ታሪክ ፡ ውስጥ ፡ አስማትና ፡ መተት ፡ ማድረግ ፡ የተለመደ ፡ ነገር ፡ ባይሆንም ፡ እንኳን ፡ እንደዚህ ፡  ለመሰሉ ፡ ነገሮች ፡ ግን ፡ እስራኤላውያን ፡ ባእድ ፡ ናቸው ፡ ማለት ፡ ግን ፡ አይቻልም ፡፡ ታድያ ፡ አምስት ፡ ተንንሽ ፡ የገብስ ፡ እንጀራና ፡ ሁለት ፡ ትንንሽ ፡ ዓሣን ፡ አባዝቶ ፡ ከአምስት ፡ ሺህ ፡ በላይ ፡ ለሆነ ፡ ሕዝብ ፡ መመገብና ፡ ዐስራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ ትርፍራፊ ፡ መሰብሰብ ፡ ከአስማትና ፡ ምትሃት ፡ ጋር ፡ ሊያገናኘው ፡ የሚችል ፡ ነገር ፡ ይኖር ፡ ይሆን ፡ እንዴ ?  እነዚህንና ፡ የመሳሰሉትን ፡ ጥያቄዎች ፡ በተለያዩ ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ሊቃውንቶች ፡ በተለያዩ ፡ ጊዜያት ፡ ሲነሱ ፡ ይደመጣሉ ፡፡ ታድያ ፡ እንደነዚህ ፡ ያሉትን ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ታሪኮች ፡ ማስተላለፍ ፡ የፈለጉትን ፡ መልእክት ፡ በሚገባ ፡ ለመረዳትና ፡ ግራ ፡ የሚያጋቡንን ፡ ነገሮች ፡ ለማራቅ ፡ ምን ፡ ዓይነት ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ያነባብና ፡ የጥናት ፡ ዘዴ ፡ መጠቀም ፡ ይኖርብናል ? ይህንን ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ክፍልስ ፡ እንዴት ፡ እንረዳዋለን ? እንደ ፡ እውነተኛ ፡ ታምር ፡ ወይስ ፡ አጠራጣሪ ፡ አስማት ?

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት